Quantcast
Channel: Kalkidantube
Viewing all articles
Browse latest Browse all 3774

በኦሮሚያ ክልል በመንግስት ላይ ሕዝባዊው ተቃውሞ ቀጥሏል-VOA Amharic

$
0
0

በኦሮሚያ ክልል የአዲስ አበባንና የፊንፊኔን ልዩ ዞኖችን ለማቀናጀት የተነደፈዉን ማስተር ፕላን በመቃወም የሚደረጉ እንቅስቃሴዎች ትላንትና በዛሬዉ እለት በጂማና በሃሮማያ ዩኒቬርሲቲዎች ተካሂደዋል፥ የመንግስት ጸጥታ አስከባሪ ሃይሎችም ተማሪዎቹን በመደብደብ ተቃዉሞዉን መበተናቸዉ ታዉቋል።
በኦሮሚያ ክልል ሕዝባዊ ተቃውሞው ቀጥሏል ጦር የዘመተበት ህዝብ መሳሪያ ከታጠቁ የመንግስት ወታደሮች ጋር ተፋጠዋል ” የታሰሩት ይፈቱ፣ ገዳዮች ለፍርድ ይቅረቡ፣ ወታደሮች ከትምህርት ቤቶች ይውጡልን፣ትምህርት ቤት የጦር ካንፕ አይደለም ፣ሰለገደላችሁን አንፈራችሁም ” የሚሉ መፈክሮችን እያሰማ ነው።
ትላንትና እና በዛሬዉ እለት በጅማና በሃሮማያ ዩኒቬርሲቲዎች ከፍተኛ ተቃውሞ ተደርጓል።
የመንግስት ጸጥታ ሃይሎችም ተማሪዎቹን በመደብደብ ተቃውሞውን መበተናቸውን ቪኦኤ ዘግቧል።በጅማ ዩኒቨርሲቲ ኪቶ ፋርዲሳ የቴክኖጂ ኢኒስቲቲዩት ተማሪዎች እሁድ ማታ በሰልፍ የአዲስ አበባ ማስተር ፕላንን አውግዘው የታሰሩ እንዲፈቱ ጥያቄ ባቀረቡበት ወቅት ሰባት መኪና ሙሉ የፌዴራል ሃይል ግቢው ውስጥ በመግባት እንደደበደባቸው ማንነቱ እንዳይገለጽ የጠየቀ ተማሪ ለቪኦኤ ገልጿል።
ተማሪዎች ድብደባውን ሸሽተው ወደ መኝታ ክፍሎቻቸው ሲሸሹ በሮችን ሰበረው በመግባት በተለይም ኦሮሞዎችን ከሌሎች ተማሪዎች ለይተው እንደደበደቡ ተማሪው ተናግሯል። ይህ በቋንቋ ለይቶ መደብደብ በኦሮሚያ ፖሊሶች እና በፌደራሎቹ መካከል ግጭት ማስነሳቱንም ተማሪው ለሬዲዮው ገልጿል። በዚሁ የኪቶ ፋርዲሳ የቴክኖጂ ኢንስቲቲዩት በተማሪዎች ላይ በተወረወረ ቦምብ 7 ተማሪዎች በጽኑ ቆስለው በጂማ ዩኒቨርሲቲ ሆስፒታል ህክምና እየተደረገላቸው መሆኑ ታውቋል። የጅማ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚደንት ዶክተር ፍቅሬ ስሜን ሰለሁኔታዉ ለመጠየቅ ቪኦኤ በእጅ ስልካቸው ላይ ደውዬ ለማግኘት ያደረኩት ሙከራ አልተሳካም ብሏል።
በተመሳሳይ በሃሮማያ በሶስት የዩኒቨርሲቲ ካምፓሶች ማለትም በቴክኖሎጂ ፣በእርሻና በእንስሰት ህክምና ትምህርት ተቋማት እንዲሁም በሃሮማያ ከተማ ሁለተኛ ደረጃ መሰናዶ ትምህርት ቤቶች ተቃውሞና የታሰሩ የፈቱ የሚለው ጥያቄ መቀጠሉን ቪኦኤ ያነጋገሩዋቸው ተማሪዎችና የአካቢው ነዋሪዎች ገልጸዋል።
በሃሮማያ 3 ካምፓሶች በቴክኖሎጂ በእርሻና በእስስሳት ህክምና የትምህርት ተቋማት ውስጥ ትናንት ማምሻው ላይ ” የታሰሩ ተማሪዎች ይፈቱ እነርሱ እስር ቤት እየተሰቃዩ ፈተና እንፈተንም”እና የመሳሰሉትን መፈክሮች በማሰማት ተቃውሞ ያደረጉ ተማሪዎች ላይ የመንግስት ወታደሮች ተኩስ ከፍተዋል ተብሏል። ከመንግስት ጥቃት ይደርስብኛል በማለት ስማቸው እንዳይገለጽ የጠየቁ ከፌደራል ፖሊስ በተጨማሪ የአግአዚ ታጣቂዎች ገብተዉ አመል የሚባል የተማሪዎች መኖሪያ ሕንጻ የሚገኝበት ግቢ ዉስጥ ከምሽቱ 4 ሰዓት የጀመሩ እስከ ንጋት 11 ሰዓት ድረስ ሲቀጠቅጡዋቸው ነበር ሲል ቪኦኤ ዘግቧል።ብዙ በጽኑ የቆሰሉ ተማሪዎች መኖራቸው ቢታወቅም በውል አጣርተን ማንነቱን አላወቅንም እንጂ የሞተ ተማሪ እንዳለ የቪኦኤ ምንጮች ተናግረዋል።
ሌላ እንዲሁ የዓይን እማኝ መሆናቸውን የተናገሩ ዛሬ ማለዳ በቴክኖሎጂ ካምፓስ ያሉ ተማሪዎች ከተሸሸጉበት ተሰብስበው ተቃውሞ ለማድረግ ሲሞክሩ፤ ውሃ በሚረጭ አድማ በታኝ መኪና እና በዱላ በመደብደብ ተማሪዎቹን እንደበተኑ ተናግረዋል።
በአለማያ ከተማ ያሉ የሁለተኛ ደረጃና የመሰናዶ ትምህርት ቤት ተማሪዎች ተቃውሞ ሲያሰሙ፤ከተማዋን ተቆጣጥረዋት የነበሩ የአጋአዚ ሃይሎች ያገኙትን ሁሉ እንደደበደቡ፣ በድብደባዉ 15 የሚሆኑ ሴቶች ተማሪዎች ከፍተኛ ጉዳት እንደደረሰባቸው ቪኦኤ ያናገራት ተማሪ ገልጻለች።
በሃሮማያ ዩኒቨርሲትና በዓለማያ ከተማ ደረሱ ስለተባሉ የተማሪዎች ድብደባ የምእራብ ሃረርጌ የፖሊስ ኮማንደር ኡስማን መሃመድ ትምህርት ቤቱ ሰላም ነው ተማሪዎች ፈተና ላይ ስለሆኑ ይልቁንስ በቤተመጻህፍት ጥናት ላይ ናቸው ሲሉ አስተባብለዋል። የቪኦኤን ሙሉ ዘገባ ያዳምጡ።


Viewing all articles
Browse latest Browse all 3774

Trending Articles