ሃምሣ ሺህ የዲቪ ዕጣዎች ተዘጋጅተዋል
እሥራኤል ውስጥ የተገደለው ኤርትራዊ የሞተው በተተኮሰበት ጥይት ምክንያት መሆኑን ቀዶ ሕክምናውን የሠሩት ሃኪም ገለጹ!!-VOA Amharic
Champions League Highlights – Matchday 3 (Tuesday), 20.10.2015
CSKA Moscow vs Manchester United 1-1 2015 All Goals and Highlights 21.10.2015 Champions League
CSKA Moscow vs Manchester United 1-1 2015 All Goals and Highlights 21.10.2015 Champions League..ዛሬ ከተደረጉት ጨዋታዎች ሲኤስኬ ሞስኮ ከማንችስተር ዬናይትድ ያደረጉትን ጨዋታ ሀይላይት ይመልከቱ።CSKA Moscow vs Manchester United 1-1 2015 All Goals and Highlights 21.10.2015 Champions League..ዛሬ ከተደረጉት ጨዋታዎች ከ ሲኤ ስ ኬኤ ሞስኮ ከማንችስተር ዬናይትድ ያደረጉትን ጨዋታ ሀይላይት ይመልከቱ
Wazema ዋዜማ Ethiopian Drama Series S02E32 Part 33
ፍትሕን በብሔር ግንኙነት የሚሸጡና ለወሲብ ድርድር የሚያቀርቡ ሙያተኞች እንዳሉ ተነገረ
ከፖሊስና ከማረሚያ ቤት በበለጠ ፍርድ ቤት ለሙስና የተጋለጠ መሆኑ ተጠቆመ
በኢትዮጵያ የፍትሕ ተቋማት ውስጥ ሙያዊ ሥነ ምግባራቸውን ጠብቀው ሕዝባዊ ኃላፊነታቸውን የሚወጡ ታማኝ የፍትሕ ባለሙያዎች ያሉትን ያህል፣ ፍትሕን በገንዘብ የሚቸበችቡ፣ የተሰጣቸውን የሙያ ሥነ ምግባር ዘንግተው ዳኝነትና
ፍትሕን በአገር ልጅነት ወይም በብሔር ግንኙነት የሚሸጡና ለወሲብ ድርድር የሚያቀርቡ እንዳሉ ተነገረ፡፡
የፌዴራል የሥነ ምግባርና ፀረ ሙስና ኮሚሽን ኮሚሽነር አቶ ዓሊ ሱሌይማን፣ ጥቅምት 9 ቀን 2008 ዓ.ም. ‹‹በኢትዮጵያ ፍትሕ ዘርፍ ሙስናን ለመከላከል የሚያስችሉ፣ የፍትሕ ዘርፍ አገልግሎት አሰጣጥና አፈጻጸም አመላካቾች›› በሚል ርዕስ በተዘጋጀው የውይይት መድረክ ላይ እንደተናገሩት፣ የተወሰኑ በፍትሕ ተቋማት ውስጥ ያሉ ሙያተኞች በተለያዩ የሥራ ዘርፎች ላይ የሚገኙና ሙስና የሚፈጽሙ ናቸው፡፡ ሙስና በተንሰራፋበት በፍትሕ መድረክ ላይ ዜጐች በእኩልነት አይስተናገዱም፡፡ በተለይም ለነፃ ገበያ ዋነኛ መሠረት የሆነው የኮንትራት አስተዳደር ከቅጥፈት፣ ከአድልዎና ከአላስፈላጊ ባህሪዎች ነፃ ሆኖ ዳኝነት መስጠት በማይቻለበት ሁኔታ፣ አገሪቱ የምትመኘውን የኢኮኖሚ ዕድገትና የሚታሰበውን ያህል ኢንቨስተሮችን መሳብ እንደማይቻል ኮሚሽነሩ አብራርተዋል፡፡ ይኼንን እውነታም ሕዝቡ ጠንቅቆ እንደሚያውቀው አክለዋል፡፡
ሙስናን የመታገያው የመጨረሻው መተማመኛ ተቋም የፍትሕ ሥርዓቱ በሙስና ከተፍረከረከ፣ አጠቃላይ የፀረ ሙስና ትግሉ አደጋ ላይ መውደቁ የማይቀር መሆኑን አቶ ዓሊ አስረድተዋል፡፡ የፍትሕ ተቋማት ከዘርፈ ብዙ የሙስና ዓይነቶች ካልፀዱ፣ አሠራራቸው ለሕዝብ ግልጽ ካልሆነ፣ በሕግ ከተቀመጠው የአሠራር ሥርዓት ያፈነገጡ በሕግ ተጠያቂ ካልሆኑ፣ ችግሩ በፍትሕ ተቋማት ብቻ እንደማይፈታና ወደ አገራዊ አደጋ እንደሚሸጋገር ሥጋታቸውን ገልጸዋል፡፡
ኮሚሽነሩ እንዳሉት፣ ሕግ መተርጐም ለዳኞች የተሰጠ ኃላፊነት ነው፡፡ ነገር ግን ዳኞች ሕግን በነፃነት እንዳይተረጉሙ ለሕዝብ ተቆርቋሪ በመምሰል የግል ፍላጐትን ለማሟላት በዳኝነት ሥራ ላይ የሚደረገው ጣልቃ ገብነት ሊወገድ ይገባል፡፡ የኮሚሽነር ዓሊን ንግግር ተከትሎ በፍትሕና ሕግ ሥርዓት ምርምር ኢንስቲትዩት ባልደረቦች ከላይ በተገለጸው ርዕስ ያዘጋጁትን ጥናት አቅርበዋል፡፡
ወ/ሪት ማዕረግ ገብረ እግዚአብሔር፣ አቶ አሮን ደጐልና ዶ/ር ደጀኔ ግርማ የተባሉት የጥናቱ አቅራቢዎች፣ ጥናታቸውን ያደረጉት ለሙስና ዋና ተጋላጭ ናቸው ባሏቸው ፍርድ ቤት፣ ዓቃቤ ሕግ፣ ፖሊስና ማረሚያ ቤቶች ላይ ነው፡፡ ጥናቱ ከድሬዳዋ ውጪ በቆዳ ስፋታቸውና በሕዝብ ብዛታቸው ቀዳሚ ናቸው ያሏቸውን ኦሮሚያ፣ አማራና ደቡብ ክልሎች፣ ውስጥ ያሉ ዋና ዋና የፍትሕ አካላትን ማካተታቸውን አስረድተዋል፡፡
ዋና ዋና ያሉዋቸው አራቱ የፍትሕ አካላት ሊፈጽሟቸው የሚችሉ የሙስና ድርጊቶች ጉቦ፣ ሥራን መበደል፣ ምዝበራ፣ በሥልጣን መነገድና የማይገባ ሀብት ማካበት መሆናቸውን ጠቁመዋል፡፡ የፍትሕ አካላቱ ለሙስና ተጋላጭ የሚያደርጓቸው ምክንያቶች ዕውቀትና ክህሎት ማነስ፣ የደመወዝና ጥቅማ ጥቅም ማነስ፣ ነፃና ገለልተኛ አለመሆን፣ ሰፊ ሥልጣን መኖር፣ ግልጽ የሆነ የአገልግሎት አሰጣጥ ሥርዓት አለመኖር በዋናነት የገለጿቸው ናቸው፡፡
ከወንጀለኞች ጋር በቅርበት መሥራት፣ ለኃላፊዎች ያላቸው መታየት ዝቅተኛ መሆን፣ ወንድማማችነት (ጥፋትን መሸፋፈን)፣ ተግባራቸው ለሕዝብ ግልጽ አለመሆን፣ ፖሊሶችን ለሙስና ከሚያጋልጡ ምክንያቶች ጥቂቶቹ ናቸው፡፡ የማረሚያ ቤቶች ጥበት፣ በታራሚዎች አያያዝ ላይ የሠራተኞቹ ግንዛቤ አናሳ መሆን፣ የማረሚያ ቤት ሠራተኞች ለሕግ ተገዢ አለመሆን፣ የጥበቃ ሠራተኞች ከታራሚዎች ጋር የሚፈጥሩት ከሙያ ውጪ የሆነ ቅርበትና ወዳጅነት ደግሞ ማረሚያ ቤትን ለሙስና ተጋላጭ ከሚያደርጉት ምክንያቶች ጥቂቶቹ መሆናቸውን ጥናት አቅራቢዎቹ ገልጸዋል፡፡
የፍርድ ቤትን አሠራር ቀልጣፋ ማድረግ፣ የፍርድ ቤት ሠራተኞችን ሥነ ምግባር ማሻሻል፣ ተጠያቂነትን ማረጋገጥ፣ ግልጽ አሠራር ማጐልበት፣ የዳኝነትን ነፃነት ማረጋገጥ፣ ከገቢ ጋር ተያያዢነት ያላቸውን ለሙስና የሚያጋልጡ ምክንያቶችን ማስወገድ፣ ተቋማትን ብቃት ባላቸው ባለሙያዎች ማደራጀት፣ የመረጃና የሰነድ አያያዝ ሥርዓት ማጠናከር፣ የክትትል ሥርዓት መዘርጋት፣ የጥቅም ግጭት ማስወገድና ሌሎችንም ለሙስና በር የሚከፍቱ ምክንያቶች በጥናቱ መለየታቸውን አቅራቢዎቹ በዝርዝር አስረድተዋል፡፡
በውይይቱ ላይ የተሳተፉት የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት፣ የከፍተኛ ፍርድ ቤት፣ የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤቶች ምክትል ፕሬዚዳንቶች፣ የማረሚያ ቤቶች አስተዳደር፣ የፌደራል ፖሊስና የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን፣ የዓቃቤ ሕግና የተለያዩ ተቋማት ተወካዮች የቀረበውን ጥናት አድንቀው አስተያየታቸውን ሰጥተዋል፡፡
ምንጭ ሪፖርተር ተጻፈ በ ታምሩ ጽጌ
Mogachoch EBS Latest Series Drama – S02E48- Part 48
Champions League Highlights – Matchday 3 (Wednesday), 21.10.2015
“ከቤት ኪራይ ባሻገ…” (ተወልደ “ተቦርነ” በየነ)
ሰሞኑን ጋዜጠኛ አርአያ ተ/ማርያም አንዲት አጭር ማስታወሻ በገጹ ላይ ከትቦ ተመለከትኩ። ጋዜጠኛ አርአያ በዲሲና እና አከባቢዋ በሚገኙ ጉራንጉሮች እየቃረመ የሚያስነብበን የተለያዩ ገጠመኞች ናቸው። እርግጥ አብዛኞቹ በግለሰብ ማንነትና ስብእና ያተኮሩ ቢሆንም በሀገረ አሜሪካ የሚኖሩ ኢትዮጲያውያን ሌላኛውን ገጽታ ለማሳየት ይጠቅማሉ ። በተለይ ሀገራችንን በወያኔ ተቀምተን ስደትን እንደአማራጭ የወሰድን ኢትዮጲያውያን “ትልቁን – ስዕል” እንዳንረሳ ከእነዚህ ውድቅዳቂ ገጠመኞች ማወቅ እንደሚጠቅመን አስባለሁ። ጋዜጠኛ አርአያም በአደገኛ ቦታዎች እየተሹለከለከ የሚያቀርበውን “ግለሰባዊ” ታሪኮች ቢገፋበት የሚያስከፋ አይደለም። እርግጥ አብዛኛው ሰው “የመንደር ወሬ” እያለ ቢያጣጥለውም እኔ ግን ከምንም ይሻላል የሚል አስተያየት አለኝ። አንዳንዶች ደግሞ “አርአያ አልቆበታል” ሲሉ ይደመጣሉ። ይህም ቢሆን ምላሹ ያለው ራሱ ጋዜጠኛው ጋር ስለሆነ ገፍቼ ልከራከር አልችልም።
በሌላ በኩል ሀገሩን በጥቂት የወያኔ ጉጅሌውች የተቀማው አብዛኛው ኢትዮጲያዊ ጋዜጠኛው ከቃረማቸው አከባቢዎች ውሎ የሚያድር አለመሆኑን መገንዘብ ያሻል። በሀገራቸው የመስራት እድል የተነፈጋቸው ኢትዮጲያውያን ከሊቅ እስከ ደቂቅ ኑሮን ለማሸነፍ የሚተጉ መሆኑ መታወቅ ይኖርበታል። በሀገር አሜሪካን የኢትዮጲያውያን አንዱ መታወቂያም የስራ ትጋታቸው እና ፍላጎታቸው መሆኑ ምስክር የሚያሻው አይደለም። በመሆኑም የዋሽንግተን ዲሲ ደቡባዊ ምስራቅ የሚገኙ አደገኛ ቦታዎች የሚውሉና የሚያዘወትሩ ጥቂት ኢትዮጲያውያን በመሆናቸው ብዙሃንን እንደማይወክሉ መገንዘብ ያሻል።
ይህ እውነት እንደተጠበቀ ሆኖ አንዳንዶች በአቋራጭ መንገድ ኑሮአቸውን ለመግፋት የሚፈልጉ ኢትዮጲያውያን አልታጡም። አቋራጭ መንገድ በራሱ መጥፎ አይደለም። ቢሆንም የምቆምበትን “ኢትዮጲያዊ ምሶሶ” በሚንዱ ተግባራት ላይ የሚመሰረት ከሆነ ለድርድር የሚቀርብ አይደለም።
እንደሚታወቀው አገዛዙ ኢትዮጲያዊነትን ለማጥፋት “ህወሀታዊ ፓሊሲ” ነድፎ ቀን ከሌት እየተጋ ነው። በምንወዳት ሀገራችን ውስጥ ኢትዮጲያዊ ምልክት የሆኑ እሴቶች እየተሸረሸሩ የግለሰቦች መጫወቻና መወደሻ እየሆኑ መሄዳቸው በግልጽ እየታየ ነው። ትላንትና አዲስ ዓመት በመጣ ቁጥር ኢትዮጲያዊ በዓል በዓል እንዲሸት የሚያደርጉት እነ ብሔራዊ እና ሀገር ፍቅር ቲአትር ቤቶች እንዲደበዝዙ ተደርገው የበአሉ ድምቀት ወሳኞቹ ግለሰቦችና ሆቴላቸው ሆኗል። ኢትዮጲያዊ አንጋፋ አርቲስቶች ወደጎን ተገፍተው (አሊያም ለባለጊዜው እንዲያድሩ ተደርገው) በደጋፊነት የሚታዩበት በዋናነት ደግሞ ከምዕራቡ አለም በዶላር ተገዝተው የሚመጡ ባህላችንን በቅጡ የማያውቁ የሚጨፍሩበት ሁኔታ ተፈጥሯል።
ከዚህ በተጨማሪ ኢትዮጲያዊ ኩራታችን እና ክብራችን ማሳያ የሆኑት ገድሎች እየቀሩ በሌላ ማንነታችን በማይገልጹ ታሪኮች እየተተካ ነው። ዛሬ በኢትዮጲያ ምድር ከ40 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ እየተደረገ የሚከበረው የካቲት 11 እንጂ የካቲት 23 አይደለም። ደደቢት አድዋን ተክቶታል። ዛሬ በኢትዮጲያ ምድር ከ25 ሚሊዮን ብር በላይ እየወጣ እንዲከበር የሚደረገው ሚያዚያ 27 ሳይሆን ህዳር 11 ሆኗል። ድላችንን የወያኔ የበኩር ልጅ የሆነው ብአዴን ተክቶታል። እውነተኛ ታሪክ እየተፋቀ አዲስ ታሪክ እየተዳፈነ ነው። ኢትዮጲያዊነት የሚታይባቸው ተቋማት እየተሸረሸሩ የቡድኖችና የዘመናችን ባለ ገንዘቦች መጨፈሪያ ሆነዋል።
ሆኖም ግን ከአገዛዙ ቁጥጥር ውጪ ባሉ ቦታዎች እንዲህ አይነት ሁኔታ እንዳይፈጠር ኢትዮጲያውያን በእልህና ቁጣ እየተንቀሳቀሱ ነው። ከዚህ አንጻር ኢትዮጲያውያን “በሰሜን አሜሪካ የኢትዮጲያውያን የባህልና ስፖርት ፌስቲቫል” የሚባለው ቅርስ በጠላቶች እጅ እንዳይወድቅ የሚያደርጉት የሞት ሽረት ትግል በምሳሌ የሚታይ ነው። ይህ የአንድነታችን እና ነጻነታችን አርማ የሆነ ፌስቲቫል በባለገንዘቦች እንዳይከፋፈል ኢትዮጲያውያን ጥረት በሚያደርጉበት ሰዓት ከከፋፋዮች ጋር መሠለፍ ወይም መሳተፍ ከዘመናዊ ባንዳነት የማይተናነስ ሀቅ ነው። “የቤት ክራይ እና የኑሮ ወጪዎች” እንደ አመክንዮ በማቅረብ አሊያም በእነሱ ድግስ ብገኝም “ባለገንዘቡን እና ባለራዕዩን አላወደስኩም” የሚል ወንዝ የማይሻገሩ ምክንያቶች የሚያስኬድ አይደለም። በእንደዚህ አይነት ፀረ- ኢትዮጲያዊ ተግባራት ከጊዜያዊ ድለላዎችና ጥቅማ ጥቅሞች በመነሳት የሚሳተፉ ኢትዮጲያውያን ሊያፍሩ ይገባል። ሊፀፀቱ ይገባል። እውነትም ሊሸማቀቁ ይገባል። እነዚህ ግለሰቦች ማህበረሠቡ ያገለላቸው የነፃነት አርማውን፣ ከትውልድ ትውልድ ሊያስተላልፍ የሚፈልገውን ቅርስ እና የኢትዮጲያዊነት ህልውናውን ሊነጥቁ ቀን ከሌት ከሚተጉ ቡድኖችና ባለ-ገንዘቦች ጋር በመተባበራቸው ምክንያት ብቻና ብቻ ነው።
ጋዜጠኛ አርአያም ትልቁን ስዕል ትቶ ማሞና መታወቂያውን ለማዛመድ የሄደበት አካሄድ ትክክል የማይሆነው በዚህ ምክንያት ነው። እንደ ግለሰብ በሸራተን መዝፈንም ሆነ በባለ ገንዘቦች ክርን ስር መውደቅ የምደግፈው አይደለም። ነገር ግን “ኢ. ኤስ. ኤፍ. ኤን. ኤ.“ እና ሸራተን አንድ አይደሉም። ለምክንያት እና መንስኤ ማነጻጸሪያ ሊሆኑ አይችሉም። ሸራተን የዘፈነ ሁሉ አልተወገዘም። ይወገዝም አልተባለም።
በተረፈ ጋዜጠኛ አርአያ “ከባለቤቱ ያወቀ ቡዳ ነው” እንዲሉ በእኔና በሰይፉ ፋንታሁን መካከል ያለውን ግኑኝነት በድፍረት መግለጽ መሞከሩ ሳያስገርመኝ አልቀረም። ያቀረባቸው መረጃዎች የጋዜጠኛውን የዛሬ ሁኔታ ብቻ ሳይሆን ትላንትና እና ነገን እንድጠራጠር አድርጎኛል። ፈጣሪ ለአሉባልታ እሩቅ፣ ለመረጃ ቅርብ ያድርገን እንዲሉ:
Welafen Drama Part 5 (ወላፈን) New Ethiopian Drama 2015
USA help rescue 70 prisoners,mainly iraqis,from “imminent excution” by ISIS.
ቴዲ አፍሮና ጎሳዬ ተስፋዬ ለምስጋና ቀን ይዘፍናሉ!
በሰሜን አሜሪካው የኢትዮጵያዊያን የስፖርትና የባህል ፌስቲቫል ላይ ከተዘጋጅት የሙዚቃ ዝግጅቶች መካከል በጉጉት ተጠብቆ በቪዛ ምክንያት ሳይደረግ የቀረው የቴዲ አፎሮና የጎሳዬ ተስፋዬ የሙዚቃ ኮንሰርት በምስጋና ቀን ለመጀመርያ ግዜ ሊደረግ ነው።
አሜሪካኖቹ Thanksgiving በሚሉት (የምስጋና ቀን ) አመት በዓላቸው ዋዜማ Nov.25.2015 በአትላንታ የተዘጋጀው የሙዚቃ ኮንሰርት ዝግጅት መጀመሩን የኮንሰርቱ አዘጋጆች ለቃልኪዳን ትዩብ የገለጹ ሲሆን፤ቴዲና ጎሳዬን ለመጀመርያ ግዜ በአንድ መድረክ ሲዘፍኑ ለመመልከት በርካቶች ይገኛሉ ተብሎ ተገምቷል።
የቃሊቲ ማረሚያ ቤት አቶ አንዳርጋቸው ፅጌ እንደሌሉ ገለፀ
በእነ ዘመነ ካሴ የክስ መዝገብ ከ2ኛ -5ኛ መዝገብ ለተከሰሱት አቶ አሸናፊ አካሉ (2ኛ ተከሳሽ)፣ አቶ ደናሁን ቤዛ (3ኛ ተከሳሽ)፣ አቶ ምንዳዬ ጥላሁን (4ኛ ተከሳሽ) እና አቶ አንሙት የኔዋስ (5ኛ ተከሳሽ) በመከላከያ ምስክርነት የተጠቀሱት አቶ አንዳርጋቸው ፅጌ ቃሊቲ ማረሚያ ቤት እንደሌሉ ማረሚያ ቤቱ ለፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ 19ኛው ወንጀል ችሎት በላከው ደብዳቤ ገልፆአል፡፡ 19ኛ ወንጀል ችሎት ሀምሌ 29/2007 ዓ.ም የቃሊቲ ማረሚያ ቤት አቶ አንዳርጋቸውን ለምን እንዳላቀረበ እንዲያብራራ፣ እንዲሁም ለምስክርነት እንዲያቀርብ ለዛሬ ለጥቅምት 12/2008 ዓ.ም ለአራተኛ ጊዜ ቀጠሮ ሰጥቶ የነበር ቢሆንም ማረሚያ ቤቱ አቶ አንዳርጋቸው ቃሊቲ እንደሌሉ በደብዳቤ አሳውቋል፡፡
ተከሳሾቹ ማረሚያ ቤቱ ሲያጉላላቸው ቆይቶ አሁን የለም ማለቱ ትክክል እንዳልሆነ የገለፁ ሲሆን 2ኛ ተከሳሽ አቶ አሸናፊ አካሉ ማረሚያ ቤቱ ምላሽ የሰጠው በአራተኛው ትዕዛዝ መሆኑን ጠቅሶ የፍርድ ሂደታቸውን ከሚገባው በላይ እያጓተተ እንደሆነ ለፍርድ ቤቱ ገልፆአል፡፡ ‹‹መከላከል ከጀመርን አንድ አመት ከስድስት ወር ሆነ፡፡ በግዞት ነው ያለነው፡፡ የሚቀርብልን ምግብ ለእንሰሳትም መቅረብ የማይገባው ነው›› ያለው አቶ አሸናፊ የማረሚያ ቤቱን ምላሽ ‹‹ፌዝ ነው›› ብሎታል፡፡
3ኛ ተከሳሽ አቶ ደናሁን ቤዛ በበኩሉ አቶ አንዳርጋቸው ፅጌን በመከላከያ ምስክርነት ሲጠቅሱ አቃቤ ህግ አቶ አንዳርጋቸው ፅጌ የሞትና የእድሜ ልክ ፍርደኛ እንደሆኑ በመጠቆም ተቃውሞ አሰምቶ እንደነበር፣ የእድሜ ልክና የሞት ፍርደኛ ቃሊቲ እንደሚታሰር ገልፆ ማረሚያ ቤቱ አቶ አንዳርጋቸው እንደሌሉ መግለፁ ‹‹የስርዓቱን ሽፍትነት ያመላክታል›› ብሏል፡፡ ‹‹የእድሜ ልክ ወይንም የሞት ፍርደኛ የት ነው የሚታሰረው?›› ሲልም ፍርድ ቤቱን ጠይቋል፡፡
3ቱ ተከሳሾች የፀረ ሽብር ግብረ ኃይሉና ጠቅላይ ሚኒስትሩ አቶ አንዳርጋቸውን እንደያዙ በቴሊቪዥን መግለፃቸውን አስታውሰው አሁንም ለሁለቱ አካላት ደብዳቤ እንደሚፅፉ ለፍርድ ቤቱ አሳውቀው የነበር ቢሆንም ከ6ኛ-9ኛ ያሉት ተከሳሾች ማረሚያ ቤቱ በፈጠረው ችግር የአቶ አንዳርጋቸውን ምስክርነት ለመስማት የፍርድ ሂደታቸው እየተጓተተባቸው በመሆኑ የአቶ አንዳርጋቸው ምስክርነት ቀርቶ ብይን እንዲሰጣቸው ጠይቀዋል፡፡
ሆኖም ግን 4ኛ ተከሳሽ አቶ ምንዳዬ ጥላሁን ‹‹ከአንዳርጋቸው ጋር ተገናኝተህ መመሪያ ተቀብለሃል ስለተባልኩ አቶ አንዳርጋቸው መጥቶ መመስከር አለበት›› ሲል አሁንም አቶ አንዳርጋቸው እንዲቀርቡለት ጥያቄውን አቅርቧል፡፡ ፍርድ ቤቱም 4ኛ ተከሳሽ አቶ አንዳርጋቸው ፅጌ እንዲቀርቡለት የሚያቀርበውን አቤቱታ ተመልክቶ ይገኙበታል ተብሎ ለታሰበው ተቋም ትዕዛዝ ለመስጠት ለጥቅምት 23/2008 ዓ.ም ቀጠሮ ሰጥቷል፡፡
ምንጭ በነገረ ኢትዮጵያ
ጋዜጠኛ ግዛው ታዬ”ክሱ የሕትመት ውጤቶቹን ለመዝጋት ታስቦ የነበረና ያለአግባብ የተመሠረተ ነው”ቃለምልልስ-VOA Amharic
የሎሚ” መፅሔት አሳታሚ የሆነው ዳዲሞስ ኢንተርቴይመንት እና የፕሬስ ሥራዎች ድርጅትና ሥራ አስኪያጁ በጋዜጠኛ ግዛው ታዬ ላይ የፌደራሉ የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት የገንዘብና የእሥራት ፍርድ ካስተላለፈ በኃላ ቪኦኤ ግዛውን አነጋግሮታል፤
ፍርዱ በሌለበት የተላለፈበት ጋዜጠኛ ግዛው ታዬ “ሲጀመርም ሆን ተብሎ የሕትመት ውጤቶቹን ለመዝጋት ታስቦ የነበረና ያለአግባብ የተመሠረተ ክሥ ነበር እራሳቸው የዘጉትን ድርጅት ከአመት በኃላ ሁለት መቶ ሺህ ብር ቀጥተነዋል ማለት ፌዝ ነው ብሏል።ሙሉ ቃለምልልሱን ያዳምጡ።
Boeing torn between Kenya and Ethiopia offices
American aircraft manufacturer Boeing is weighing options of opening an office either in Kenya or Ethiopia to gain a foothold in the eastern Africa market.Boeing Company senior vice president Marc Allen said Thursday the US giant is assessing factors like human resource, infrastructure and existing frameworks for partnerships in the two capitals.
The Boeing executive has been on a fact-finding tour of South Africa, Nigeria, Kenya and Ethiopia aimed at paving the way for entry into the three corners of sub-Saharan Africa.
The US giant, which is the supplier of Kenya Airways and Ethiopian Airlines’ fleet of Dreamliners and other Boeing planes, currently has a presence in North Africa.
“Talent and comparative advantage will guide us in our choice of location in the region,” Mr Allen said on the sidelines of an American business forum in Nairobi on Thursday.
Kenya and Ethiopia have recently been racing to attract foreign direct investments into their economies with creation of special economic zones and promises of lower costs of doing business including cheap electricity.
Mr Allen said the firm’s areas of interest include research, engineering and analytics.
Boeing projects that air traffic for Africa’s carriers would grow at an average of 5.7 per cent per year between 2015 and 2034 – ahead of the global average of 4.9 per cent.
“Boeing forecasts that African carriers will need 1,170 new airplanes valued at approximately $160 billion (Sh16.3 trillion) over the next 20 years,” he said.
businessdailyafrica.com
Ethiopian Airlines Dreamliner declares emergency over the Atlantic after one of its engines ‘shuts down’
Flight 500 had set out from Dublin Airport around 6am this morning
However less than two hours into flight, plane encountered problems
Pilot signalled emergency and turned around to land back in Ireland
A Dreamliner declared an emergency this morning over the Atlantic after one of its engines shut down.
The Ethiopian Airlines flight had set out from Dublin Airport at 6am this morning bound for Washington Dulles, when it encountered problems over the Atlantic Ocean.
The pilot was forced to turn the plane around and signal an emergency, and declare intention to return to Ireland.Speaking to MailOnline Travel Ben Grossman-Cohen, who was on the flight, said: ‘We took off and they were serving food about an hour into the flight. Then the flight map showed that they had turned back east and the updated arrival time was just an hour away.
‘Then they told us there was a minor technical issue and they were returning to Dublin to address it and they’d update us later. Maybe 10-15 minutes later they said there was an issue with the left engine and we’d be landing in Dublin and they’d tell us more later.’
The Boeing 787-8 Dreamliner made a safe landing, with sources claiming the reason for the emergency was because one of the plane’s twin jet engines had ‘shut down.’
The passenger jet touched down at 8.35am.The Irish Mirror are reporting there were 300 people on board.
Flight 500 had originally set out from Addis Ababa, and was heading to the U.S, via Dublin.
A replacement plane has been sent out from Frankfurt in Germany, with the passengers expected to continue on to Washington at around 1pm local time.
A spokesperson for Dublin Airport told MailOnline Travel: ‘Ethiopian Airways had a technical/transit stop with one of its aircraft to refuel before it headed onward to Washington this morning.
‘The aircraft left at 6.10am and at 7.45am we had reports that the aircraft was returning with a technical issue.
‘The aircraft landed safely just after 8.30am. Passengers have disembarked and I understand the aircraft is undergoing an inspection.’
MailOnline has also contacted Ethiopian Airlines and is awaiting a response.
The plane’s variants seat 242 to 335 passengers in typical three-class seating configurations. Ethiopian Airlines has 13 Dreamliners in its fleet.
Interview with the former Ethiopian VP Fiseha Desta – Pt 1- SBS Amharic
Tamrat Desta – Selina (ሰሊና) New Ethiopian Music Clip 2015
ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ በቤተሰብ እንዳይጎበኝና ስንቅ እንዳይገባለት ተከለከለ- VOA Amharic
ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ በቤተሰብ እንዳይጎበኝና ስንቅ እንዳይገባለት ተከለከለ..በእሥር ላይ የሚገኘው ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ በቤተሰብ እንዳይጎበኝና ስንቅ እንዳይገባለት መከልከሉን ወንድሙና ጠበቃው ከቪኦኤ ጋር ባደረጉት ቃለምልልስ ገለጹ።ሙሉ መረጃውን ያድምጡ።..ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ በቤተሰብ እንዳይጎበኝና ስንቅ እንዳይገባለት ተከለከለ