Celebrating Ethiopian Meskel in Dubai
ethiopian woman stabbed on bus makes first trip ho- (ALEMNEH WASSE NEWS)
አፍሪካ ፊልም አካዳሚ አዋርድ ላይ”ሦስት ማዕዘን”ፊልም በሽልማት ተንበሸበሸ (ቴዎድሮስ ጌታሁን)
ትላንት ማምሻውን በውቢቷ ፖርት ኤልዛቤት ከተማ በተካሄደው አስራ አንደኛው የ አፍሪካ ፊልም አካዳሚ አዋርድ ላይ፣ በ
ስምንት ዘርፎች እጩ ሆኖ የቀረበው የ ቴዎድሮስ ተሾመ “ሦስት ማዕዘን” ፊልም በ ሦስት ዘርፎች አሸናፊ በመሆን ታሪክ ሰራ።
Triangle going to America ወይም ሦስት ማዕዘን የመጀመሪያ ሽልማቱን ያገኘው ምርጥ የማጀቢያ ሙዚቃ
በሚለው ዘርፍ ሲሆን በዚህም ድምፃዊ ጌትሽ ማሞ ወደ መድረክ በመውጣት የተዘጋጀለትን ሽልማት ተቀብሏል
በዚህ ዘርፍ የናይጄሪያዎቹ ታዋቂ ፊልሞች A place in the star, Iyore እንዲሁም የ አንጎላው Queen of angole እና
የሞሪታኒያው Timbectu እጩ ሆነው ቢቀርቡም ሦስት ማዕዘን ፊልምን ያጀበው ጌትሽ ማሞን ሚቆመው አልተገኘም ቀጥሎ በምርጥ ተዋናይ ዘርፍ በተካሄደ ውድድር አሁንም ሦስት ማዕዘን ፊልም አሸናፊ መሆን ችሏል
በዚህ ዘርፍ የደቡብ አፍሪካው I number number, የናይጄሪያው October, የ ካሜሮኑ Leperdes እና የ ኮትዲቫሩ Run ፊልሞች ላይ በመሪ ተዋናይነት የተወኑ አርቲስቶች ቀርበው በመጨረሻም ኢትዮጵያዊው አክተር ሳምሶን ታደሠ ቤቢ አሸናፊ መሆን ችሏል
ሽልማቱን ለመቀበል ወደ መድረክ የወጣው ሳምሶን ንግግሩን በአማርኛ ያደረገ ሲሆን በዚህም “…ስለሁሉም የረዳኝን
እግዚአብሔር አመሰግናለሁ እዚህ ደረጃ ደርሳለሁ ብዬ በህይወቴ አስቤ አላውቅም ነበር አሁን ደስታዬ ወደር የለውም
በመጨረሻ ዓለም ወደደም ጠላም አፍሪካ አንድ ትሆናለች” ብሏል
የ አማርኛውን ንግግር ወደ መድረክ በመውጣት ወደ እንግሊዝኛ የተረጎመለት የፊልሙ ደራሲ’ና ፕሮዲውሰር ቴዎድሮስ ተሾመ
ነበር ቀጥሎ በ ሽማግሌዎች ወይም በ እንግዶች ምርጮ የ አፍሪካ ምርጥ ፊልም በሚል ዘርፍ Le president ካሜሩን Timbectu ሞሪታኒያ October ናይጄሪያ Run ኮትዲቮር እና I number number ደቡብ አፍሪካ በ እጩ ዘርፍ ቀርበው አሁንምኢትዮጵያዊው ሦስት ማዕዘን ፊልም አሸናፊ መሆን ችሏል ይህን ሽልማት ለመቀበል ደራሲ እና ፕሮዲውሰር ቴዎድሮስ ተሸሞ መሪ ተዋንያኖቹ ሳምሶን ታደሠ ቤቢ እና ሰለሞን ቦጋለ እንዲሁም የ ማጀቢያ ሙዚቃውን የሠራው ድምፃዊ ጌትሽ ማሞ ወደ መድረክ በመውጣት ሽልማቱን ከተቀበሉ በኋላ የ ዶክተር አርቲስት ጥላሁን ገሠሠን ኢትዮጵያ ሀገሬ የሚለውን ዜማ በጋራ ከተመልካቹ ጋር በማቅረብ ታዳሚውን ማዝናናት ችለዋል።
Ethiopia’s Samson Tadesse received _Best Supporting Actor_ at AMAA
Ethiopia’s Samson Tadesse received _Best Supporting Actor_ at AMAA…ሳምሶን ታደሰ (ቤቢ) በአፍሪካ ፊልም አካዳሚ አዋርድ ላይ የ”ሦስት ማዕዘን” ፊልን ረዳት ተዋናይ ከሆነ በኃላ የተናገረው።Ethiopia’s Samson Tadesse received _Best Supporting Actor_ at AMAA…
ደመራው ሲደመር
ኃይለ ገብርኤል ብሩክ መስከረም ከባተ በኋላ ከሚመጣው የመስቀል ደመራ ጋር ልዩ ትዝታ አለው፡፡ ‹‹ኢዮሃ አበባዬ መስከረም ጠባዬ፤ መስከረም ሲጠባ ወደ አዲስ አበባ›› እየተባለ የሚዘመርበት ጊዜን፣ በተለይ መስከረም 16 ቀን
በቀዳማዊው ኃይለ ሥላሴ ዘመን በመስቀል አደባባይ ሲከበር የነበረውን ልዩ ልዩ ሥነ ሥርዓቶች ያስታውሳል፡፡ አከባበሩ እንደዘመነ ደርግ በ‹‹አብዮት አደባባይ›› ወይም በዚህኛው ዘመን በመስቀል አደባባይ ብቻ የተወሰነና የታጠረ አልነበረም፡፡
በወቅቱ ደመራው በብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ቴዎፍሎስ ከተባረከና ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ከለኮሱት በኋላ ከመንፈሳዊው ሥነ ሥርዓት ጎን ለጎን በሥነ በዓሉ ላይ የተገኙት ከከተማዋ የተለያየ ኅብረተሰብ ክፍል የተውጣጡ የሰልፍ ትርዒት የሚያሳዩበት ነበር፡፡ የክብር ዘበኛ፣ የጦርና የፖሊስ ሠራዊት በችቦ የታጀበ የሰልፍ ትርዒት ሲያሳዩ፣ መኩሪያ የተሰኘው የንጉሠ ነገሥቱ አንበሳ የተቀመጠበት ሰረገላ ደግሞ በፊት መሪነት በንጉሠ ነገሥቱ ፊት እያለፈ ይጓዝ ነበር፡፡ በዳግማዊ ምኒልክ ጎዳና እስከ ስድስት ኪሎ ድረስ ግራና ቀኝና በየጥጋ ጥጉ ቆሞ የሚመለከተውን የበዓሉ ተሳታፊንም ሰላምታ እየሰጡ ያልፋሉ፡፡
በተለይ ከ50 ዓመት በፊት ከየመንግሥት መሥሪያ ቤቱ የተውጣጡ ከተሜዎች የሚንቦለቦል ችቦ ይዘው ይሰለፉ የነበሩት ሁሉም እጀ ጠባብ የባህል ልብስ ለብሰው ነበር፡፡ ታዳጊ ወጣቶችም ነጭ ሸሚዝና ነጭ ቁምጣ ሱሪ አድርገው በምድር ጦር ማርሽ ታጅበው ስለመስቀሉ ክብር እየዘመሩ ከጦር ኃይሎች ወደ መስቀል አደባባይ ያመሩ እንደነበር ኃይለ ገብርኤል ያስታውሳል፡፡
በአራተኛው ምእት ዓመት፣ በንግሥት እሌኒ አማካይነት ክርስቶስ ኢየሱስ የተሰቀለበት መስቀል መገኘቱ የሚታሰብበት የመስቀል ደመራ በዓል፣ በኢትዮጵያ ለሁለት ሺሕ ግድም ዓመታት ሲከበር ኖሯል፡፡ የበዓሉን ሃይማኖታዊ፣ ባህላዊና ትውፊታዊ ገጽታ የተመለከተው ዓለም አቀፉ የትምህርት የሳይንስና የባህል ድርጅት (ዩኔስኮ) የዓለም የማይዳሰስ ባህላዊ ቅርስ አድርጎ ከመዘገበው ሁለት ዓመት ሆኖታል፡፡
ክብረ በዓሉ በአማራና በትግራይ ‹‹መስቀል›› ሲባል፣ በተለያዩ ብሔረሰቦች እንደየአካባቢው ቋንቋ የተለያየ መጠርያ አለው፡፡ ለምሳሌ በኦሮሞ ‹‹ጉባ›› ወይም ‹‹መስቀላ››፣ በሀድያ፣ በወላይታ፣ በዳውሮ፣ በጋሞ፣ በጎፋ ‹‹መስቀላ››፣ በከምባታ ‹‹መሳላ››፣ በየም ‹‹ሔቦ››፣ በጉራጌ ‹‹መስቀር››፣ በካፊቾና ሻኪቾ ‹‹መሽቀሮ›› ይባላል፡፡
ምንነቱ
የመስቀል ክብረ በዓል በአብዛኞቹ የኢትዮጵያ ሕዝብ ዘንድ በታላቅ ድምቀት የሚከበር ብሔራዊ በዓል ነው፡፡ የመስቀል በዓል አጀማመር የክርስትና እምነት መሠረት የሆነው ኢየሱስ ክርስቶስ የተሰቀለበት መስቀል፣ በ4ኛው መቶ ክፍለ ዘመን ከተቀበረበት ተቆፍሮ መገኘትና በተለይም የመስቀሉ አንድ ክንፍ ወደ ኢትዮጵያ መጥቶ በግሸን ዐምባ መቀመጥ ጋር ቀጥተኛ የሆነ ቁርኝት ቢኖረውም፣ እያንዳንዱ ብሔረሰብ በዓሉን የሚያከብርበት እንደባህሉ፣ አኗኗሩ፣ ወጉ፣ ኢኮኖሚያዊና ማኅበራዊ ገጽታው የራሱ መንገድ አለው፡፡
የመስቀል በዓል መለያው ደመራው ነው፡፡ ደመራ ንግሥት እሌኒ፣ ክርስቶስ የተሰቀለበትን መስቀል ከተቀበረበት ለማውጣት በኢየሩሳሌም ቀራንዮ በሚባል አካባቢ በጎልጎታ ቁፋሮ ያስጀመረችበትን ቀን ለማሰብ የሚከበር ሥነ ሥርዓት ነው፡፡ የደመራ ሥነ ሥርዓቱ በመጠኑም ቢሆን ከቦታ ቦታ ይለያያል፡፡ በአክሱም፣ በዓዲግራት፣ በላስታ፣ ላሊበላ፣ በዋግ ሕምራ፣ በከፊል ጎጃምና በአዊ ዞን ደመራው መስከረም 16 ቀን ቢደመርም ሥርዓተ ጸሎቱ የሚካሄደውና ደመራው የሚለኮሰው መስከረም 17 ቀን ንጋት ላይ ነው፡፡ በአንፃሩ አዲስ አበባን ጨምሮ በሸዋና በከፊል ጎጃም፣ በሐዲያ፣ በጉራጌ፣ በሸከቾ፣ ካፊቾ፣ ኮንታ ደመራው የሚበራው በዋዜማው መስከረም 16 ቀን ምሽት ነው፡፡ የደመራው አደማመርና አበራር ሥነ ሥርዓት ግን በሁሉም የኢትዮጵያ አካባቢዎች ከሞላ ጎደል ተመሳሳይ ነው፡፡
የመስቀል ደመራ በዓል በብሔራዊ ደረጃ የሚከበረው በአዲስ አበባ በመስቀል አደባባይ ሲሆን፣ እዚህ ደመራ የሚደመረውና ሥርዓተ ጸሎት ተደርጎ የሚቀጣጠለው መስከረም 16 ቀን ወደ ማታ ነው፡፡ በዚሁ በዓል ላይ በመቶ ሺዎች የሚቆጠሩ የአገር ውስጥና የውጭ ታዳሚዎች ይገኙበታል፡፡ ዘንድሮ በተለይ የግብፅ ኮፕቲክ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን ፓትርያርክ ፖፕ ቴዎድሮስ ዳግማዊ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ባደረጉላቸው ግብዣ መሠረት በክብረ በዓሉ ይገኛሉ፡፡
የፌዴራል ፖሊስ ባንድ የሰልፍ ትርዒትና በዘመናዊ መሣሪያ በመታገዝ ልዩ ልዩ ጣዕመ ዝማሬን ያሰማል፡፡ ሠረገላ ይነዳል (ይጐተታል)፡፡ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ፣ ፓትርያርክ ወርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ በዓሉን በተመለከተ ትምህርትና ቡራኬ ከሰጡ በኋላ ደመራውን ባርከው ችቦ በእሳት በማያያዝ በሥነ ሥርዓቱ ላይ ከሚገኙ ከፍተኛ የመንግሥት ባለሥልጣን ጋር በመሆን ደመራውን ይለኩሳሉ፡፡
ደመራው ወደ አመድነት እስኪለወጥ ይነዳል፡፡ በዚሁ ወቅት ሕዝቡ ‹‹ኢዮሃ አበባዬ መስከረም ጠባዬ›› በማለት ይዘፍናል፡፡ ሴቶች እልል ይላሉ፡፡ ደመራው የተጸለየበትና የተባረከ ስለሆነ ሕዝቡ አመዱንና ትርኳሹን እየተሻማ ወደቤቱ ይዞ ይሄዳል፡፡ አንዳንዶቹ በአመዱ ግንባራቸው ላይ የመስቀል ምልክት ያበጃሉ፡፡ አመዱ ለሰውም ሆነ ለከብቶች ፍቱን መድኃኒት ነው የሚል እምነት አለ፡፡ በደመራው ማግስት መስከረም 17 ቀን በሚከበረው ዋናው የመስቀል በዓል ምዕመኑ ቤተ ክርስቲያን አስቀድሶ ከተመለሰ በኋላ ሲበላና ሲጠጣ፣ ከጎረቤትና ዘመድ አዝማድ ሲገባበዝና ሲጠያየቅ በፍቅርና በደስታ በዓሉን ሲያከብር ይውላል፡፡
የምርቃት ሒደት
ክብረ በዓሉን ከሚገልጹት ባህላዊ መገለጫዎች አንዱ ምርቃት ነው፡፡ ለዓይነት የስድስቱን ብሔረሰቦች አመራረቅ ከተለያዩ ምንጮች ያገኘነውን እነሆ፡፡
በሀዲያ
ደመራ የሚቀጣጠለው መስከረም 16 ሲሆን፣ መጀመሪያ በዕድሜ ትልቅ የሆኑ በየመንደሩ ያሉ አዛውንቶች ‹‹እንኳን በሰላም አደረሰን እንኳን በሰላም ብርሃን አየን ከጨለማም ወጣን›› እያሉ በመመረቅ ችቦ ይለኩሳሉ፡፡ ከዚያም ወጣቶች እየተጫወቱ ደመራውን ይዞራሉ፡፡ ሲነጋጋ ከብቶች ደመራውን ይዞራሉ፡፡
በወላይታ
ጨዋታው ሲያበቃ ለመስቀል የታረደውን በሬ እየተመገቡ ይመራረቃሉ፡፡ ‹‹እስከ መጨረሻው እንኖራለን የዳሞታ ተራራ እንደኖረ፣ የኮይሻ ተራራ እንደኖረ እኛም እንኖራለን፡፡ አህያ ቀንድ እስኪያወጣ እንኖራለን፡፡ ኮንድቾ በጣም አጭር እንጨት ምሰሶ እስከሚሆን እንኖራለን፤›› እያሉ መጪውን ዘመን በተስፋ በመቀበል ይለያያሉ፡፡
በሸከቾ
በበዓሉ ቀን ጧፍ በማብራት በየጓዳው በየእህል ማስቀመጫው ይዞ በመግባት ‹‹መጥፎ ነገር ከቤት ውጣ፣ ሀብት ግባ›› እያሉ ከመረቁ በኋላ ጎረቤት ተጠራርቶና ተሰባስቦ ችቦ ይበራል፡፡ በነጋታው የእርድ ሥርዓት የሚከናወን ሲሆን ቤተሰብና ጎረቤት በመስቀል ይጠራራል ይገባበዛል፡፡
በየም
በዋዜማው ሌሊት ሊነጋ አቅራቢያ ‹‹የረሀብ ምንቸት ውጣ ጥጋብ ግባ›› በማለት ችቦ ከተለኮሰ በኋላ ወደ ደመራው ቦታ ሁሉም ያመራል፡፡ ደመራው በአዛውንቶች ተመርቆ ይለኮሳል፡፡
በካፍቾ
የደመራ በዓሉም የሚከበረው በባህላዊ እምነት መሪው ግቢ ውስጥ ሲሆን እያንዳንዱ ሰው ችቦ በየቤቱ ለኩሶ በራሱ ቤት ዙሪያ በመዞር ድህነት ውጣ፣ ሀብት ግባ ብሎ መልካም ምኞቱን ከገለጸ በኋላ የተቀጣጠለውን ችቦ የባህላዊ እምነት መሪው ግቢ በተዘጋጀው ደመራ ላይ ወስዶ ይለኩሳል፡፡ በማግስቱ ሠንጋ ይታረድና የደመራው እሳት በነደደበት ቦታ ላይ እሳቱን ለማቀዝቀዝ ሲባል ደም ይፈስበታል፡፡ እያንዳንዱ ሰው ደሙን በእጁ በመንካትና ከአመድ ጋር በመለወስ ግንባሩ ላይ ይቀባል፡፡
በጎፋ
ማስቃላ ዮ! ዮ! እያሉ የተለያዩ የበረከት ሀሳቦችን ይለዋወጣሉ (መስቀል እንኳን መጣህልን) ማለት ነው፡፡ አስከትለውም እየደጋገሙ ማስቃላ ዮ! ዮ! ዳናው ዳና አልባ ዙማዳን ዳና (አልባ ዙማ በአካባቢው የሚገኘው ትልቅ ተራራ ሲሆን እንደሱ እንኖራለን እንደ ማለት ነው፡፡) ክንቲ ሻላዳን ዳና (ክንቲ ሻላ ማለት በአካባቢው የሚገኘው ትልቁ አለት ሲሆን እንደሱ እንኖራለን እንደ ማለት ነው፡፡) መሪናው ዳና (ለዘለዓለም እንኖራለን) ማለት ነው፡፡ ሀረይ ካጨ ከሳናዳን (አህያ ቀንድ እስከሚያበቅል ድረስ እንኖራለን፡፡) ገላኦ ገል ውራናስ ዳና (ሁሉም ልጃገረዶች እስኪያገቡ ድረስ እንኖራለን)፡፡ እንዲህ እያሉ እርስ በርስ ይሸካከማሉ ይተቃቀፋሉም፡፡
የመስቀል በዓል በተለያዩ የአገሪቱ ክፍሎች፣ በገጠርም በከተማም፣ በደብርም በገዳምም እንደ ኅብረተሰቡ ባህልና ልማድ በታላቅ አክብሮት በየዓመቱ ይከበራል፡፡ እንዲያውም በአንዳንድ ብሔረሰቦች እንደ ካፊቾ፣ ወላይታ፣ ሸክቾ፣ ኮንታ ያሉት እንደዘመን መለወጫ ይቆጥሩታል፡፡ በተለይ መረጃዎች እንደሚያሳዩት፣ በሸከቾ በመሽቀሬ ባሮ በዓል ላይ ደመራ ነዶ ሲያበቃ አስራ ሁለት ጉማጅ እንጨቶችን ከውስጡ በመልቀም ስልቻ ውስጥ ያስቀምጡና አንድ ወር ባለፈ ቁጥር አንድ ጉማጅ እየተጣለ ከአሥራ ሁለት ላይ ሁለት ጉማጆች ብቻ ሲቀሩ የዘመን መለወጫ በዓል እየደረሰ መሆኑንና ድግሱ ከወዲሁ መጀመር እንዳለበት ኅብረተሰቡን ያሳስቡታል፡፡
የኢትዮጵያውያን የመስቀል በዓል አከባበር ከተቀረው የዓለም ክፍል የተለየ፣ ወቅቱም ክረምቱ አልፎ የበጋ በመሆኑ በዓሉ ካለው ሃይማኖታዊ ፋይዳ ባሻገር በርካታ ማኅበራዊ ጠቀሜታዎች እንዳሉት ይጠቀሳል፡፡
መስቀል በዓልን ባለም ቅርስነት ባስመዘገበው የቅርስ ጥናትና ጥበቃ ባለሥልጣን መረጃ መሠረት፣ ዓመቱን በሙሉ ተለያይተው የኖሩ የቤተሰብ አባላትና ዘመዳሞች የሚገናኙበትና የሚጠያየቁበት፣ ማኅበራዊ ችግሮቻቸውን የሚፈቱበትና የሚረዳዱበት፣ ወጣቶች የሚተጫጩበትና ራሳቸውን ለጋብቻ የሚያዘጋጁበት፣ በጋብቻ የተሳሰሩ ቤተሰቦች የሚጠያየቁበት፣ የተጣሉ ግለሰቦች፣ ቡድኖች እና በጥል የተለያዩ ባልና ሚስቶች ባጠቃላይ በተለያዩ አጋጣሚዎች የተፈጠሩ አለመግባባቶችን በመፍታት እርቅ የሚወርድበትና ሰላም የሚሰፍንበት ነው፡፡
መስቀል፣ በማኅበረሰቡ አባላት መካከል ያለውን ግንኙነት በማጠናከር የጎላ ድርሻ የሚያበረክት፣ እንደ ቤተሰብና አካባቢው በአዲሱ ዓመት የሚሠሩ ሥራዎች ተለይተው እንዴት መሠራት እንዳለባቸው የሚመከርበትና የሚታቀድበት፣ በአንዳንድ አካባቢዎች እዳ የሚሰረዝበትም ነው፡፡
ወጣቶች በአባቶች የሚመረቁበት፣ ጎልማሶች ዕውቀትን ከአባቶች የሚቀስሙበት፣ ኃላፊነት የሚረከቡበት፣ ለኢትዮጵያ ሠላምና ብልጽግናን በመመኘት ጸሎት የሚደረግበት፣ ሕዝቡ የሚዘፍንበት፣ የሚጨፍርበት፣ የሚደሰትበት፣ ግጥም የሚገጥምበት ድምፁን የሚያሟሽበት፣ ወጣቱ የሚኮራበት፣ ባህሉን የሚያጠናበት፣ የሚለወጥበት ወቅትና በአጠቃላይም ቤተ ክርስቲያን ለበዓሉ ከምትሰጠው ሃይማኖታዊ ትርጉምና ሥርዓት በመነሣት በበርካታ ብሔረሰቦች ዘንድ ጥልቅ የሆነ የመተሳሰብ፣ የፍቅር፣ የወዳጅነት መንፈስ የሚጎለብትበት ወቅት መሆኑ ከፋይዳው ይጠቀሳሉ፡፡
በዓሉን በተመለከተ በኢንቬንተሪም ሆነ በጥናትና ምርምር የተገኙ ዕውቀቶችንና ልምዶችን በሥርዓተ ትምህርት ውስጥ ማካተት፣ የሀገር ሽማግሌዎችና አዋቂዎች ስለመስቀል በዓል ቅርስ ምንነትና ጠቀሜታ ባገኙት አጋጣሚ ሁሉ ለወጣቶች ማስተዋወቅ እንዲችሉ ማመቻቸት ለቅርሱ ቀጣይነት እየተደረጉ ያሉ እንክብካቤዎች መሆናቸውን ባለሥልጣኑ አመልክቷል፡፡
ምንጭ ሪፖርተር ተጻፈ በ ሔኖክ ያሬድ
Balageru MirT was amazing!-Zewdy AWAlOM
Balageru MirT was amazing! all of the contestants did so wonderfully! I am so grateful that everything worked out in the end! I am so thankful to God that I finally made it to Ethiopia and had the chance to perform! and on TV,
too! shout out to Abraham Wolde for having me on his show, and shout out to Rozy Negusei for initiating my involvement in this event! I thank my gracious and ever-supportive parents for traveling to Ethiopia to be here with and for me! and last but not least, I want to thank all of my fans! you have been supporting me from afar from the day you found me on YouTube! it is truly an honor and a blessing from God that I was able to come HOME to perform for you!
Dawit Tsige Winner of Balageru Mirt – Last and Amazing Performance-1
Dawit Tsige Winner of Balageru Mirt – Last and Amazing Performance – Video 2
Dawit Tsige Winner of Balageru Mirt – Last and Amazing Performance – Video 2…ዛሬ ፍጻሜውን ባገኘው የ”ባላገሩ አይድል” የድምጽ ውድድር ዳዊት ጽጌ አሸናፊ ያደረጉት ሁለት ሙዚቃዎች ይመልከቱ።..Dawit Tsige Winner of Balageru Mirt – Last and Amazing Performance – Video 2…
Interview with Singer Hachalu Hundessa-SBSAmharic
Interview with Singer Hachalu Hundessa-SBSAmharic….ሀጫሉ ሁንዴሳ በኦሮምኛ ቋንቋ ተወዳጅ ከሆኑ ድምጻውያን መሀል ይጠቀሳል። ሀጫሉ ሥርጭቱን ከአውስትራሊያ ካደረገው SBS ራዲዮ አዘጋጅ ካሳሁን ሰቦቃ ጋር በአማርኛ ስለ ሙዚቃ ሕይወቱ ቃለ ምልልስ አድርጓል። ለመግቢያ ያህል የሀጫሉን ዘፈን አድምጠው ወደ ቃለ ምልልሱ ይሻገሩ።
Esayas Tamira Finished 2nd at Balageru Mirt – Watch Last Live Performance- Video 1
Esayas Tamira Finished 2nd at Balageru Mirt – Watch Last Live Performance -Video 2
Esayas Tamira Finished 2nd at Balageru Mirt – Watch Last Live Performance -Video 2….የመጨረሻው ደቂቃ ድረስ የአሸናፊነት ግምት የተሰጠው በባላገሩ ምርጥ ሁለተኛ ሆኖ ያጠናቀቀው ኢሳያስ ታምራት ያቀረባቸውን ሁለት ሙዚቃዎች ሊንኩን ተጭነው ቪዲዮዉን ይመልከቱ።Esayas Tamira Finished 2nd at Balageru Mirt – Watch Last Live Performance -Video 2..
የሮማዉ ሊቃነ ጳጳሳት አቡነ ፍራንሲስ የአሜሪካ ጉብኝታቸዉን አጠናቀቁ-VOA Amharic
ርእስ ሊቃነ ጳጳሳት ፍራንስስ በፊላዴልፊያ ጉብኝቻቸዉ ትላንት እሁድ ማለዳ ላይ ካረፉባቸዉ አቡኖች እጅግ ሞቅ ያለ ከፍተኛ አቀባበል ተደርጎላቸዋል። አባ ፍራንስ ቀድም ብሎ በካቶሊክ ቀሳዉስት የጾታ ጥቃት ከደረሰባቸዉ አምስት ሰዎች ጋር በግል ተገናኝተዋል።
Interview with Prof Lapiso Getahun Delebo – Pt I – SBS Amharic
Interview with Prof Lapiso Getahun Delebo – Pt I – SBS Amharic…ፕሮፌሰር ላጲሶ ጌታሁን ዴሌቦ፤ ስለ ዳኣማት ሥርወ መንግሥትና ሥልጣኔ ይናገራሉ። የዳኣማት ሥርወ መንግሥት፤ የኢትዮጵያ የመጀመሪያው ሥርወ መንግሥት እንደሆነ የሚያብራሩት የታሪክ ምሁሩ ከኤስቢኤስ ራዲዮ ጋር ያደረጉትን ኢንተርቪው የመጀመሪያ ክፍል ያድምጡ።
Teddy Afro’s Concert for Mesqel Cancelled
Tewodros Kassahun’s (a.k.a. Teddy Afro) fans are in for yet another disappointment with the cancellation of a postponed concert for Mesqel, the Ethiopian Christian holiday of “the Finding of the True Cross”.
Fans had hoped that Ethiopia’s sensational but controversial singer and song writer would perform inside Laphto Mall, after his earlier plan for a concert during the eve of Ethiopia’s New Year was thwarted due to lack of a permit from the city administration.
“Though the organisers had submitted a written notice for the aborted New Year’s Eve concert, the City was unable to accommodate their request on that specific date due to overlapping programmes that had overstretched our capacity,” Feleke Negash, head of Cabinet Affairs Directorate of the Addis Abeba City Administration, told Fortune last week. “As such we communicated this to them that it would be better to hold the event at some other time.”
Organisers had agreed to postpone the concert to Mesqel, while managers from both Ballers Lounge and AZ Entertainment had confirmed this to Fortune two weeks ago. The announcement of the postponement of the ill-fated concert to Mesqel put fans in a frenzy of inflated expectations surrounding the situation.
For the New Year’s Eve concert, an estimated 6,000 fans were expected to flock to Laphto Mall to be entertained by Teddy Afro’s captivating music, with its uniquely popular melodies and often nostalgic lyrics, which are at times highly divisive and politically charged.
For Yehualashet Chane, a 30-plus, fan of Teddy Afro, the cancellation of the concert was a huge disappointment.
The fans would have paid 700 Br for tickets, while VIP seats would cost 1,200 Br. Judging by some of the comments made by the fans, price was not an issue. Rather, some expressed the view that the venue might be too small to accommodate the large number of fans, given the following the singer enjoys. As Abrham Wondimu complained on social media, that venue is a “small place” to host Teddy’s fans.
Another fan, Ephrem Abebe, posted on Teddy Afro’s Facebook page expressing his excitement about the concert.
“I will attend the concert of my #1 favorite musician for the first time,” he said.
The anticipation of the fans was widespread, and Kirubel Kinfe in excitement, posted “can’t wait!” on the singer’s official Facebook page.
As the date of the concert approached though, Teddy Afro apologised for the inconvenience due to cancellation. His fans took to social media to express their anger directed at city authorities and show support for their musical idol.
“It’s okay,” a fan named Hailu Belay posted on Facebook. “The most important thing is that you [Teddy Afro] are well.”
Another fan, Surafel Teklu, turned to one of the singer’s popular songs for inspiration, “It’s going to be easy – Kelal Yihonal.”
Following the cancellation of the New Year’s Eve concert, fans found comfort in the pledge made by the singer that, “God willing, the concert will take place on Mesqel.”
However, Teddy Afro’s trademark “Love Shall Triumph – Fiqir Yashenifal” slogan will not be echoing across Laphto Mall this Sunday. A representative of the organisers visited the city administration last week twice, but without a letter of request, said officials in the city administration.
“We asked him to produce such letter and he has not returned,” Feleke told Fortune.
The City enforces a directive for those interested in organising public gatherings and events, balancing their right to hold the event, while safeguarding security in case any brawls arise, according to Feleke.
Organisers were not responsive last week, despite repeated efforts to reach them for comment. Contrary to the level of curiosity by some of the singer’s fans about whether or not a concert would take place during Mesqel, neither Teddy Afro’s website, nor his social media platforms has made an announcement.
“The cancellations reflect badly on the organisers,” Alazar Ahmed, a marketing and promotion expert, told Fortune.
addisfortune.net/
Zuckerberg To Bring Internet To Refugee Camps
Mark Zuckerberg has said he will help the United Nations bring the internet to refugee camps.
The Facebook founder and CEO made the announcement as he addressed the UN Private Sector Forum.
“Connectivity will help refugees better access support from the aid community and maintain their links to families,” he said.Mr Zuckerberg called for universal internet access to be made a global priority.
He said wide internet access “needs to be at the heart of the global development strategy” to address new challenges and needs of the new generation.
In the long term, Facebook will help UN agencies develop tools to track progress toward implementing the development goals, Mr Zuckerberg said.
“Data can help us make smarter decisions but only if you can interpret it quickly and with confidence, so we want to help the UN make decisions that will advance our goals,” he added.
The UN adopted a new set of 17 development goals on Friday designed to end poverty and hunger and fight inequality over the next 15 years.
Mr Zuckerberg and his wife Priscilla were seen in public at the weekend when they attended a White House state dinner for Chinese President Xi Jinping.
Source news.sky.com/