Quantcast
Channel: Kalkidantube
Viewing all 3774 articles
Browse latest View live

የኤርትራ ካቶሊካዊት ቤተክርስትያን ሊቀ-ጳጳስ አቡነ መንግሥተአብ ተስፋማርያም ከርዕሰ-ሊቃነ-ጳጳሳት ዘካቶሊካዊያን አባ ፍራንሲዝ ጋር ሆነው በዩናይትድ ስቴትሱ ጉዞ ላይ እየተሣተፉ ናቸው፡፡- VOA Amharic

$
0
0

የኤርትራ ካቶሊካዊት ቤተክርስትያን ሊቀ-ጳጳስ አቡነ መንግሥተአብ ተስፋማርያም ከርዕሰ-ሊቃነ-ጳጳሳት ዘካቶሊካዊያን አባ ፍራንሲዝ ጋር ሆነው በዩናይትድ ስቴትሱ ጉዞ ላይ እየተሣተፉ ናቸው፡፡- VOA Amharicየኤርትራ ካቶሊካዊት ቤተክርስትያን ሊቀ-ጳጳስ አቡነ መንግሥተአብ ተስፋማርያም አሜሪካንን እየጎበኙ ከሚገኙት የሮማው ርዕሰ-ሊቃነ-ጳጳሳት አባ ፍራንሲስ ጋር ሆነው በዩናይትድ ስቴትሱ ጉብኝት ላይ እየተሣተፉ ናቸው፡፡
ዛሬ ፕሬዚደንት ባራክ ኦባማ ባደረጉት ንግግር “እኔም የስደተኞች ልጅ ነኝ ፤ይህቺ አገር ሰደተኛ ልጆች የሚኖሩባት አገር ነች”ማለታቸው ልብ ይነካል የሚሉት የኤርትራ ካቶሊካዊት ቤተክርስትያን ሊቀ-ጳጳስ አቡነ መንግሥተአብ ተስፋማርያም ከቪኦኤ ጋር በአማርኛ ቋንቋ ያደረጉትን ቃለምልልስ ያዳምጡ።


Eid Al Adha Arefa Holiday on EBC – FilFilu Comedy-Part 1

$
0
0

Eid Al Adha Arefa Holiday on EBC – FilFilu Comedy-Part 1…..Eid Al Adha Arefa Holiday on EBC – FilFilu Comedy-Part 1….በዛሬው ዕለት የኢድ አል አድሀ በዓል ሲከበር ፍልፍሉ ያቀረበውን የኮሜዲ ስራ በመመልከት ዘና ይበሉ።…Eid Al Adha Arefa Holiday on EBC – FilFilu Comedy-Part 1.

Eid Al Adha Arefa Holiday on EBC – FilFilu Comedy Part 2

$
0
0

Eid Al Adha Arefa Holiday on EBC – FilFilu Comedy Part 2…..Eid Al Adha Arefa Holiday on EBC – FilFilu Comedy Part 2….በዛሬው ዕለት የኢድ አል አድሀ በዓል ሲከበር ፍልፍሉ ካቀረበው የኮሜዲ ስራ ሌላኛዉን በመመልከት ዘና ይበሉ።….Eid Al Adha Arefa Holiday on EBC – FilFilu Comedy Part 2

Benyam and Isaac Kinde Featured as “10 Scientists Who Are Making Their Mark”

$
0
0

New York (TADIAS) — Science News magazine has named brothers Benyam and Isaac Kinde among the world’s ten up-and-coming scientists who are likely to make lasting impact in their fields.

“To identify some of the early-career scientists on their way to more widespread acclaim, Science News surveyed 30 Nobel Prize winners to learn whose work has caught their attention.” the magazine said announcing the list. “From those names, Science News editors chose 10 to feature in this special report. All have demonstrated high-caliber research leading to noteworthy achievements.”

The-Kinde-brothers-kalkidantube

The older brother Isaac Kinde, 31, who serves as Chief Scientific Officer at Baltimore-based biotechnology startup PapGene, “credits his supportive family and years of hard work for his scientific success,” Science News highlights. “His tenacity is probably fueled by his active lifestyle — he’s an avid biker — and his devotion to coffee, which he says is rooted in his family’s Ethiopian culture. ‘It’s almost in our blood. I can’t literally say that, because I’m a scientist,’ Kinde says. ‘But, almost.’” Science News adds: “PapGene’s sensitive technologies are based on tests Kinde helped develop as a graduate student at Johns Hopkins University, where he studied with cancer researcher Bert Vogelstein. Spotting cancer early requires finding a few rare, cancer-associated genetic alterations among large amounts of normal DNA. That’s made more difficult by the DNA reader’s error rate. Kinde and colleagues created a way to chemically label and mass-copy sections of DNA to identify the real mutations.”

Benyam Kinde, 27, is studying how genetic modifications affect brain activity at the cellular level. “Many people view the brain as the last frontier of human health research. We still don’t know very much about how individual cells in the brain coordinate the activity of higher-level function that defines us as humans,” Benyam tells Science News. “This mystery is one that Kinde, an M.D./Ph.D. student at Harvard Medical School and MIT, aims to solve. He is interested in how chemical modifications of DNA affect brain function, focusing on a protein nicknamed MeCP2. When this protein is damaged or missing, it changes the activity of multiple genes and causes Rett syndrome, a disorder marked by developmental delays, seizures and autism-like behaviors.”
Tadias Magazine
Read more at ScienceNews.com »

Welafen Part 2 (ወላፈን) New Ethiopian Drama

$
0
0

Welafen Part 2 (ወላፈን) New Ethiopian Drama……ወላፈን አዲስ ተከታታይ ድራማ ክፍል 2
Welafen Part 2 (ወላፈን) New Ethiopian Drama 2015.. ይመልከቱ።….Welafen Part 2 (ወላፈን) New Ethiopian Drama….ወላፈን አዲስ ተከታታይ ድራማ ክፍል 2
Welafen Part 2 (ወላፈን) New Ethiopian Drama 2015.. ይመልከቱ።.

የ5 አመቷ ሶፊያ አለም አቀፍዊ መልእክተኛ እና ጀግና ሆነች (ታምሩ ገዳ)

$
0
0

የሮማው ካቶሊክ ቤ/ክ ሊቀ ጳጳስ የሆኑት አቡነ ፍራንሲስ በአሜሪካ የሚያደረጉትን የ 6 ቀናት ጉብኝታቸውን ለማደረግ እሮብ እለት ከቀትር በሁዋላ ወደ ዋሽንገተን ዲሲ ጎራ ሲሉ ከተቀበሏቸው ታላላቅ መሪዎች (ፕ/ት ኦባማን እና ቤተሰቦቻቸው ጨምሮ) ይልቅ 11ሚለዮን ሰዎችን በመወከል ከካሊፎርኒያ /ሎሳንጀለስ ከተማ ድረስ ተጉዛ ፓፓውን በግንባር ያገኘችው የ 5 አመቷ ሶፊያ ክሩዝ ትልቅ አለም አቀፍዊ የዜና ሽፋን ለማግኘት እና ታሪካዊት ልጃገረድም ለመሆን ችላለች።

12038290_10154343013379298_5638655577720123207_n
ስፊያ አሜሪካ ውስጥ በመወለዷ ሙሉ የአሜሪካ ዜግነት ያላት ሲሆን ከጎረቤት ሜክሲኮ በህገወጥ መንገድ የመጡት ወላጆቿ ግን ህጋዊ ሰንድ የላቸውም። ታዲያ በአሜሪካ ህግ መሰረት በማነኛውም ጊዜ ሊባረሩ የሚችሉት ወላጆቿ እና መሰል 11 ሜሊዮን ሰደተኞች ጉዳይ እንቅልፍ የሚነሳት ሶፊያ አባቷን ጨምሮ ከጥቂት አክቲቪስቶች ጋር በመሆን ለአቡነ ፈራንሲስ ደህንነት ሲባል ልዩ እና እጅግ ጥብቅ የጸጥታ ቁጥጥር ወደ ነበረበት የ ዋሽንግተኑ ስለፍ ላይ ከተገኙት በአስር ሺዎች የሚቆጠሩ የብጹነታቸው አፈቃሪዋች እና ምእመናን ጋር በመቀላቀል የፓፓውን መምጣት ይጠባበቁ ነበር።ታዲያ አቡኑ ወደ ሕዝቡ ሰቃረቡ ትንሿ ሶፊያ የደህነነት ጥበቃው አጥርን በማቋረጥ ወደ አቡነ ተንቀሳቃሽ መኪና መሮጧን የተመለከቱ የደህንነት ጥበቃዎች ሶፊያን ለማገድ/ለመከለከል ቢሞክሩም ሁኔታውን የተመለከቱት አቡነ ፈራንሲስ በምልክት ”ጨቅላ ህጻኑዋን ወደ እኔ ትመጣ ዘንድ አትከልክሏት” በማለታቸው የተነሳ ከጥቂት ደቂቃዎች በፊት በጽጥታ ሃይሎች የተዋከበችው እና የተገፈተረችው ሶፊያ ከጥቂት ደቂቃዎች በሁዋላ በነዚያ ባዋከቡዋት የጥበቃ ሰራተኞች በአንደኛው እቅፍ ተይዛ አቡነ ፍራንሲስ ከቆሙባት ግልጽ አውቶ ሞቢል በመቅረብ የበጹነታቸውን አባታዊ ቡራኬያቸውንም አግኝታለች።
የትንሿ ሶፊያ እና የ ፓፓው ድንገተኛ ግንኙነት በዚህ ብቻ አላበቃም ። የወላጆቿ ከአሜሪካ ምድር የመባረር ሰጋት ከልቧ የገባዋ ሶፊያ በእጇ የጻፈችው ደበዳቤ ለብጹነታቸው በግንባር ተገኝታ በእጇ ሰጥታለች። መልእክቱም በከፊል “ብጹ አቡነ ፍራንሲስ ውሰጤ በእጅጉ ማዘኑን ለገልጽሎት እፈልጋለሁ።እንደማንኛውም ሰው ከወላጆቼ ጋር የመኖር መብት እንዳለኝ አምናለሁ፣ ደስተኛ የመሆን ተፈጥሮአዊ መብት አለኝ፣ የእኔን ቤተሰቦችን ጨምሮ ሁሉም ሕገ ወጥ ሰደተኞች ለአሜሪካ ህዝብ ካሮት ፣ብርቱካን ፣ሽንኩርት ፣ጎመን እና የመሳሰሉትን በማብቀል እና ለገበያ በማቅረብ ልዩ አስተዋጽኦ በማደረጋቸው ተገቢው ክብር እና ሰብእና ሊሰጣቸው ይገባል፤ብጹነቶ ወላጆቼ በማንኛውም ጊዜ ከአሜሪካ ምድር ሊባረሩብኝ ሰለሚችሉ እባክዎትን ፕ/ት ኦባማን ሆነ ኮንግረሱን አቋማቸውን እንዲቀይሩ ተማጸኑልኝ ”ይላል። ከጽሁፉም በተጨማሪ ፓፓው በግራ እና በቀኝ እጆቻቸው የተለያዩ ዝርያ ያላቸው ህጻናት “የቱንም ያህል ቀለማችን ቢለያይም እኔ እና ጓደኞቼ እንዋደዳለን” የሚል የግርጌ ማስታወሻ ተጽፎበት ይገኛል።የሶፊያ ወላጅ አባት የሆነው ራዎል ክሩዝም ከጉብኝቱ በሁዋላ “ አቡነ ፍራንሲስ የእግዜአብሔር መልክተኝእበመሆናቸው ልጄ ብጹነታቸውን በግንባር አግኝታ መባረኳ በራሱ ተአምር ነው።” ብሏል።

ትንሿ ሶፊያም የ11 ሚሊዮን ሰንድ አልባ ሰደተኞች ሰጋት እና ጭንቀት የሆነው በአሜሪካ ምድር በሰላም ሰርቶ የመኖር ሕጋዊ መብትን ለ76 አመቱ ፓፓ ከማደረሰ በተጨማሪ በዙዎች በቅርብ ርቀት ሊያዩዋቸው የሚመኙት አቡነ ፈራንሲሰን ጥምጥም ብላ ለመሳም እና በእጃቸውም ለመባረክ እድሉን አግኝታለች። የሶፊያ መልእክትን በጥሞና የተረዱት እና ሁሌም የሚያነሱት አባ ፍራንሲስ ሐሙስ እለት ከ አሜሪካ ኮንግረስ አባላት ፊት ቀረበው ባሰሙት ንግግር”እኔም የሰደተኞች ልጅ ነኝ፣ሰደተኞችን አንፍራቸው፣ አንግፋቸው። በአንድ ወቅት ሁላችንም እንግዶች/ሰደተኞች ነበረን።”በማለት መንፈሳዊ እና አባታዊ ምክራቸውን ሰጥተዋል። በመደረኩ ላይ የነበሩት በተለይ አፈጉባኤው(ካቶሊኩ) ጆን ቢይነር እንባቸው ልውረደ ፣አልውረድ እያለ ሲተናነቃቸው ተስተውለዋል።ከብዙ ሰደተኞች ቤተሰቦች እንደተገኙ የሚናገሩት አብዛኞቹ የአሜሪካ ኮንግረስ ኣባላትም “በአንድ ወቅት ሁላችንም እንግዶች ነበርን !”የሚለው የኣቡነ ፍራንሲስ አባባል ለጊዜውም ቢሆን ከልባቸው ዘልቆ የገባ የመሰላል።የሶፊያ ሆነ የብጹነታቸው ሰጋት እና መልእክትም ከምድረ አሜሪካ ውጪ የሚገኙ በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ሰደተኞች ወቅታዊ እና አስከፊው ሁኔታን ማመላከቱ አይቀረም።

Gigi,Ethiopia needs to hear from you! -(ALEMNEH WASSE NEWS)

$
0
0

Gigi,Ethiopia needs to hear from you! -(ALEMNEH WASSE NEWS)…..Gigi,Ethiopia needs to hear from you! -(ALEMNEH WASSE NEWS)…..Gigi,Ethiopia needs to hear from you! -(ALEMNEH WASSE NEWS)……Gigi,Ethiopia needs to hear from you! -(ALEMNEH WASSE NEWS)….Gigi,Ethiopia needs to hear from you! -(ALEMNEH WASSE NEWS)

ALI MOHAMMED BIRRA –“Eshurrururu Ya Birtukanewo”

$
0
0

ALI MOHAMMED BIRRA – “Eshurrururu Ya Birtukanewo”…ALI MOHAMMED BIRRA – “Eshurrururu Ya Birtukanewo”…..ALI MOHAMMED BIRRA – “Eshurrururu Ya Birtukanewo”….ALI MOHAMMED BIRRA – “Eshurrururu Ya Birtukanewo”……ALI MOHAMMED BIRRA – “Eshurrururu Ya Birtukanewo”


Arsenal breaks new ground in Ethiopia

$
0
0

Arsenal Football Club has become the first Premier League side to secure a regional partnership in Ethiopia after announcing Dashen Brewery as its Official Beer Partner.
The three-year-partnership will help Arsenal get closer to its fans in Ethiopia and will focus on supporting Dashen Brewery’s community based initiatives with coaches from the club taking part in grassroots football development projects in Ethiopia.
Dashen Brewery will also directly engage with supporters in Ethiopia through the club’s digital platforms, promotional activities and marketing initiatives featuring Arsenal first-team players and club legends.

Arsenal chief commercial officer Vinai Venkatesham said: “Arsenal has a huge fanbase across Africa, and our support in Ethiopia stands out as particularly strong. We are delighted to be partnering with Dashen Brewery, together creating the first regional partnership for a Premier League club, in this rapidly growing and developing territory.”
The partnership follows backing from overseas shareholders of Dashen Brewery (Duet and Vasari).
Dashen Brewery chief executive officer Devlin Hainsworth added: “We are truly excited about this partnership. Dashen & Arsenal share common values with community being at the heart of both brands. This partnership will see Dashen invest both in grassroots football while at the same time supporting our commitment to creating meaningful consumer experiences.”
source arsenal.com

Bekenat Mekakel Part 22 (በቀናት መካከል) New Ethiopian Drama

የአርበኞች ግንቦት ሰባት አመራር አቶ ነዓምን ዘለቀ ለአድማጭ ጥያቄዎች የሰጡት መልስ-VOA Amharic

$
0
0

የአርበኞች ግንቦት ሰባት የዓለም አቀፍ አመራር የዉጭ ግንኙነት ሃላፊና የንቅናቄዉ ምክር ቤት አባል አቶ ነአምንን ዘለቀ በዝግጅቱ ላይ ለአድማጮች በሰጡት መልስ የአገር አድን ጥምረት ንቅናቄ የተፈጠዉ በኢትዮጵያ ስልጣን ለመያዝ ሳይሆን በስልጣን ላይ ያለዉን መንግስት አስወግዶ አገሪቱን ለዴሞክራሲያዊ አስተዳደር ለማመቻቸት ነዉ ብለዋል።

አብዮቱና ትዝታዬ (ኮ/ል ፍሥሓ ደስታ)፣ አዲስ መጽሃፍ – አዲስ ምስጢር(ቅኝት ክንፉ አሰፋ)

$
0
0

የመጽሐፉ ርእስ፣ አብዮቱና ትዝታዬ
ደራሲ፣ ፍሥሓ ደስታ (ኮ/ል)
አሳታሚ፣ ፀሐይ አሳታሚ ድርጅት
የገጽ ብዛት፣ 598 ገጾች
ዋጋ፣ $44.95

(ቅኝት ክንፉ አሰፋ)

ፀሐይ አሳታሚ ድርጅት ከዚህ ቀደም ሁለት የአብዮቱ መጽሃፍቶችን አበርክቶልናል። የኮ/ል መንግስቱ ኃ/ማርያም – “ትግላችን” እና ሻምበል ፍቅረ ስላሴ ወግደረስ – “እኛና አብዮቱ”። የኮ/ል ፍሥሓ ደስታ “አብዮቱና ትዝታዬ” ከቀድሞዎቹ ትንሽ ለየት ይላል። ኮ/ል ፍሥሓ ደስታ ተድበስብሶ የቆየውን የወታደራዊ መንግስት ውስጣዊ ገመና ብቻ ፈልፍለው አላቀረቡም። በአብዮቱ ሂደት ለተከሰቱ ጥፋቶች ከራሳቸው ጀምረው ተጠያቂው የሆነው ወገንን ከማመልከትም አልታቀቡም። ደራሲው ብዙ ምስጢሮችንም ያስነብቡናል።Fisseha Desta’s book

12025570_131112877242143_1246105835_n
መጽሃፉ ዳጎስ ያሉ ምዕራፎች ይዟል። በአምስት ክፍሎች የተመደቡ አስራ አምስት ምእራፎች ተካትተውበታል። ከቅድመ 1966 ዓ.ም. ፖለቲካዊ እንቅስቃሴ፣ በደራሲው አገላለጽ – እስከ የ”መጨረሻዋ እራት” የነበሩትን ሂደቶች በስፋት ይቃኛል። ባጭሩ በአፄው መንግሥት ላይ የተነሱ ዓመፆችን በቀላል አማርኛ እያስነበበ የአብዮቱን አፈጣጠር፣ “የየካቲት አብዮት ከነገሌ እስከ መሿለኪያ” በሚል ምዕራፉ ያስነብበናል። ስለ አብዮቱ ውስብስብ ሂደት፤ ስለ ነጭና ቀይ ሽብር፣ የሶማሊያ ወረራ፣ የሕወሓት እንቅስቃሴ፣ የኤርትራ ችግር፣ የግንቦት 8 መፈንቅለ መንግሥት ሙከራ … በስፋት ያወጋና በመጨረሻዎቹ ምዕራፍ ግዙፉ ሠራዊት ለምን እንወደቀ ይነግረናል።

ጸሐፊው ኮ/ል ፍሥሓ ደስታ ከ1967-1983 ኢትዮጵያን ባስተዳደረው ወታደራዊ መንግስት እስከ ምክትል ፕሬዚዳንትነት የዘለቀ ሥልጣን ነበራቸው። ከ1983 በኋላ ለሃያ ዓመታት በእስር ቆይተዋል። በመጽሐፋቸው ረጅሙ የህይወት እና የሥራ ተመክሯቸውን በመንተራስ፤ በቡድን ለስላጣን ባለቤትነት ከተደረጉ ሽኩቻዎች እስከ ሀገራዊ የመሪነት ግዴታዎችን መወጣት፣ ከግድያና የጥልፍልፎሽ ሴራዎች እስከ የሥር ነቀል አዋጆች ውጥንና አተገባበር፣ ከሙያ ጓዶቻቸው ድብቅ ስብዕና እስከ የውስጥና የውጭ ጣልቃ ገብነቶች፣ የአገርን ክብርና ሉዓላዊነት ለማስጠበቅ የተደረጉ እልህ አስጨራሽ ትግሎችና የውድቀቶቻቸው መንስኤዎች ወዘተ በስፋት ዳስሰዋል።

አብዮት ራስዋን እየበላች በነበረበት ሰሞን የእነ ጀነራል ተፈሪ ባንቲ የአገዳደል ሁኔታ የሚገልጸው ክፍል የአንባቢን ቀልብ ከሚስቡት ክፍሎች ውስጥ አንዱ ነው። ኮ/ል ፍሥሓ ደስታ ሁኔታውን በዚህ መጽሃፋቸው እንዲህ በማለት ይተርኩታል።

“…ኮ/ል መንግሥቱ ጠመንጃቸውን እንዳነገቱ ብቅ ብለው በደንብ ከተመለከቱን በኋላ “ትክክል ነው” ብለው ተመለሱ። የመጡትም ቀደም ብለው ማን መቅረት ማን መገደል እንዳለበት በወሰኑት መሠረት ስህተት እንዳይፈጠር ለማረጋገጥ እንደነበር ግልፅ ነው።

ከጥቂት ቆይታ በኋላ መጀመሪያ ወደነበርንበት የስብሰባ አዳራሽ ተጠራን። ወደዚያ ስናመራ ኮ/ል ተስፋዬ ገብረኪዳንን “ባለፈው ጄኔራል አማን ተገደሉ አሁን ደግሞ ሥራቸውን ከሚሰሩበት ቦታ አምጥተን፣ ራሳችን ሾመን እንዴት እኒህ ሽማግሌ [ጄነራል ተፈሪ] ይገደላሉ? ስለዚህ ለመንግሥቱ እንንገራቸው” አልኩትና ተያይዘን ወደቢሯቸው ገባን። እኛም የመጣንበትን ስንነግራቸው “እውነታችሁን ነው” በማለት የውስጥ ስልክ አንስተው ከደወሉ በኋላ መነጋገሪያውን እያስቀመጡ “አዝናለሁ ጓዶች አልቋል” ብለው ነግረውን እያዘንን ወደ ስብሰባው አመራን። እንደገባን ኮ/ል መንግሥቱ መጥተው “ስለሁኔታው ለጦሩ ማስረዳት ስላለብኝ ኮ/ል ተስፋዬ ገብረኪዳን ከኔ ጋር እንድትሄድ” በማለት ጠየቁ። ኮ/ል ተስፋዬም “በማዛቸው ወታደሮች ፊት እጄን ሰቅዬ ወጥቼ ጦሩን ለማነጋገር ፈጽሞ ሕሊናዬ ሊቀበለው ስለማይችል አልሄድም፤ እንደውም ወደክፍሌ እመለሳለሁ” አለ። እኔም “ከእንግዲህ በዚህ ዓይነት እዚህ ግቢ ለመሥራት ፍላጐት የለኝም እኔም እንደተስፋዬ ወደክፍሌ መመለስ እፈልጋለሁ” አልኩ። መንግሥቱም ሽጉጣቸውን በማውጣት “ይህን እርምጃ ባልወስድ ኑሮ ሁላችንም አልቀን ነበር፤ በድያችሁ ከሆነ ግን ግደሉኝ” በማለት ሽጉጡን ጠረጴዛው ላይ ወረወሩት…”

በወቅቱ ከነበሩት ሁለቱ ተቀናቃኝ ፓርቲዎች፤ በኢሕአፓ እና በመኢሶን ላይ ጸሃፊው የሰጡት አስተያየት ኮ/ል መንግስቱ ኃ/ማርያም እና ሻምበል ፍቅረ ስላሴ ወግደረስ ካስነበቡን ትንሽ ለየት ይላል። ኮ/ል ፍሰሃ፤ የሁሉንም ፓርቲዎች ብቃት ያወድሳሉ፣ የአመራሩን ችግሮች ደግሞ ይወቅሳሉ። እንዲህ በማለት፣

“…የኢሕአፓ ቆራጥነት፣ የመኢሶን የርዕዮተ-ዓለም ብስለትና የደርግ ሀገር ወዳድነት ተጣምሮ አገሪቱን ወደ ላቀ ደረጃ ሊያደርስ ይችል የነበረ ኃይል በአመራሮቹ ስህተት ያለአግባብ እርስ በርሱ ተጨራርሷል።”

ደራሲው በወታደራዊው መንግስት አመራሩ ውስጥ ከፍተኛ ሚና ይጫወቱ የነበሩ በመሆናቸው በወቅቱ በነበሩ ስህተቶች ከሃላፊነት ነጻ ያለመሆናቸውንም እንዲህ ሲሉ ገልጸዋል።

“… ኢትዮጵያ ትቅደም! ያለምንም ደም!’ ብለን በተነሣን ማግሥት… እነዚያ ለሀገራቸው የለፉትንና የደከሙትን አዛውንቶች መጦር ስንችል ገደልናቸው።”

ይህንን መጽሃፍ ከቀድሞዎቹ የአብዮቱ መጽሃፍት ለየት የሚያደርገው ደራሲው እንደ ጲላጦስ ከደሙ ነጻ ለመሆን የሌሎቹን ጥፋቶች ብቻ እየኮነኑ የጻፉት አለመሆኑ ነው። ራሳቸውን ከመውቀስ፣ ይቅርታ እስከመጠየቅ መድረሳቸው ደግሞ ከወገንተኝነት የራቁ መሆነቸውን ያሳየናል። ለዚህም ነው “… በማወቅ፣ በድፍረት፣ ባለማወቅና በስህተት ለተፈጸሙት ደግሞ ሙሉ ሃላፊነትን በመውሰድ በበኩሌ የኢትዮጵያን ሕዝብ ይቅርታ እጠይቃለሁ።…” ያሉት።

ከመጽሐፉ ድንቅ ትረካዎች መካከል የተወሰኑት ማቅረቡ ሰለ መስጽሃፉ ለአንባብያን ፍንጭ ሊሰጡ ይችላሉ። አንዳንዶቹ መረጃዎች ከዚህ ቀድመው አልተሰሙም። ፍጹም አዲስ ናቸው። ለምሳሌ የፓትሪያርኩን ማምለጥ በተመለከተ ከዚህ ቀደም የሰማነው ነገር አልነበረም። መጽሃፉ እንዲህ ይላል፣

… ፓትርያርኩ እንደሌሎቹ እስረኞች ሳይሆን ብሔራዊ ቤተመንግሥት በሚገኘው የአድሚራል እስክንድር መኖሪያ ቤት በቁጥጥር ስር እንዲውሉ ተደረገ። በታሰሩ በጥቂት ቀናት ግን ጠባቂዎቻቸው መነኩሴ ስለሆኑ የትም አይሄዱም ብለው ሲዝናኑ ቆባቸውን አውልቀው፣ ጺማቸውን ተላጭተውና ልብሳቸውን ለውጠው በግዮን ሆቴል በኩል ወጥተው ጠፉ። መጥፋታቸው እንደተነገረም በደርግ ውስጥ ከፍተኛ ድንጋጤ ተፈጠረ። …

ደርግ በዓሉን በሚያከብርበት ወቅት የወቅቱ የደርጉ ሊቀመንበር ጀ/ል ተፈሪ ባንቴ በአብዮት አደባባይ ንግግር አድርገው ነበር። በንግግራቸውም ለኢሕአፓ ጥሪ አድርገዋል። አብዮት አደባባይ የነበረው አከባበር እንዳለቀ የሕዝብ ድርጅት አባላት ኮ/ል መንግስቱን እንዴ እንዳዋከቡዋቸው ሲጽፉ፣

…የሕዝብ ድርጅት አባላት መስፍን ካሡ፣ ነገደ ጐበዜ፣ እንዳርጋቸው አሰግድ፣ ሰናይ ልኬ እና ሌሎችም ወደተቀመጥንበት ቦታ እያለከለኩና እየሮጡ መጡ፤ ኃይሌ ፊዳም ተከተለ። ምነው ጓድ መንግሥቱ እርስዎን አምነን ተሰብስበን ኢሕአፓ አየገደለን አላስጣላችሁን፤ ይባስ ብላችሁ ደግሞ እኛን የበለጠ ለማስመታት ለኢሕአፓ ጥሪ እንዴት ታደርጋላችሁ ብለው ከግራ ከቀኝ ያዋክቧቸው ጀመር። መንግሥቱም አንዴ ይቅርታ አድርግልኝ ብለው ኃይሌ ፊዳንና የተቀሩትን ይዘው ቡና ቤት ውስጥ ወደምትገኘው አነስተኛ ሣሎን ገቡ። በዚያች ቀንና ሰዓት መንግሥቱ የተነጠቁትን ስልጣን ለማስመለስ መኢሶን ደግሞ ኢሕአፓን በማስመታት ለሥልጣን መንገዱን ለመጥረግ ሴራ ሳይጠነሰስ አልቀረም።…

ቀይ ሽብርን መኢሶኖች እንደጀመሩት እና የጀመሩትም ከኢሕአፓ ነጭ ሽብርና ግድያ ራሳቸውን ለመከላከል እንደሆነ ጽፈዋል። ‘ብሳና ይነቅዛል ወይ ቢሉት ለዛፎች ሁሉ ማን አስተማረና’ እንደተባለው በአብዮቱ ሰፈር ደግሞ ቀይ ሽብር የሚለውን መፈክር በቲዎሪም በተግባርም ለደርግ ያስጨበጠው መኢሶን መሆኑ አገር ያወቀው ጸሐይ የሞቀው ሀቅ በመሆኑ ቃላትን በማውገርገርና ነገሮችን በማድበስበስ ከዚህ የታሪክ እውነታ ለማምለጥ መሞከር ትርፋ ትዝብት ነው።…’ ይላል።

ይህንን በመኢሶኖች ተጀመረ ያሉትን ቀይ ሽብር ኮሎኔል መንግስቱ ሃይለማርያም እንዳስቆሙት “አብዮቱና ትዝታዬ” ይነግረናል። እንዲህ ሲል፣

… መንግሥቱ ፊታቸው ተለዋወጠ። “ግድየለም እኔ መንግሥቱ ብቻዬን አስቆመዋለሁ፤ ከእንግዲህ እኔ ሳላውቅና ሳልፈቅድ አንድም ሰው አይገደልም” በማለት ከስብሰባው ወጥተው አንድ ሁለቴ ሲጋራቸውን አቦነኑና ወደ ቢሮአቸው ሄዱ። እውነትም እንዳሉት ከመጋቢት 30፣ 1970 ጀምሮ ቀይ ሽብርም ሆነ ነፃ እርምጃ ቆመ። ኮ/ል መንግሥቱ ይህንን ማድረግ የቻሉት በኢማሌዲህ ሥራ አስፈጻሚ ሰብሳቢነታቸው እንዲሁም በርዕስ መንግሥትና የርዕሰ ብሔር ሥልጣናቸው ተጠቅመው እንደሆነ ግልፅ ነው። ዛሬ አንዳንዶች ሊመፃደቁ አንደሚሞክሩት ሳይሆን ቀይ ሽብርን ሊያስቆም የሚችል ከሳቸው ውጭ አንዳችም ኃይል አልነበረም።…

መጽሃፉ እንዲህ እያለ የአስራ ስባት አመቱን የኢትዮጵያ ፖለቲካ ሂደት በአዳዲስና አስገራሚ መረጃቆች እያዋዛ እስከመጨረሻዋ ሰዓት ያዘልቀናል። የመጨረሻዋ እራት በምትለው ምእራፍ ኮሎኔል መንግስቱ በሚስጥር የያዙትን ስንብትና ከሃገር ጥለው የመሄድ ምስጢር፣

… ግንቦት 10፣ 1983 ቅዳሜ ማታ በጡረታ የተገለልነውን፣ በአዲሱ ካቢኔ ያልተካተቱት፣ እንደዚሁም አዲስ የተሾሙት በተገኙበት በፕሬዚደንቱ መኖሪያ ቤት ለኛ መሸኛ ለአዲሶቹ መቀበያ የእራት ግብዣ ተደረገ። … በዚህ ግብዣ ላይ ከወትሮው በተለየ የታዘብኩት ቢኖር ፕሬዚደንቱ አምቦ ውሃ ብቻ ሲጠጡ ስላየኋቸው ለምን እንደማይጠጡ ስጠይቃቸው ጤንነት ያልተሰማቸው መሆኑን ገለፁልኝ። ወደኋላ ተመልሸ ሳስበው ግን ሆድ ያባውን ብቅል ስለሚያወጣው አገር ጥለው ስለመሄዳቸው ሚስጢር እንዳያመልጥ ለጥንቃቄ ያደረጉት ነበር። ግብዣው እንዳለቀ ቤታቸው በራፍ ላይ ቆመው አንድ በአንድ እየጨበጡ አሰናበቱን። ዳግም ላንገናኝ የመጨረሻዋን እራት በልተን ተለያየን።…

ሲሉ ገልጸዋል።

የኢትዮጵያ አብዮት ሰፊና ውስብስብ የነበረ ቢሆንም በግላቸው ተካፋይ የነበሩበትን፣ በዓይናቸው ያዩትንና በማስረጃ ያረጋገጧቸውን እውነታዎች በተቻለ መጠን ከወገናዊነት በፀዳ መልኩ በዚህ መጽሐፍ ለማቅረብ ሞክረዋለሁ።

ጸሃፊው የታሪክ ባለሞያ አይደሉም። ታሪክን፤ በተለይ ባለሙያ ያልሆኑ ሰዎች ሲጽፉ ወገንተኝነት ጉዳይ መነሳቱ አይቀርም። ከሰው ስህተት አይጠፋምና መጽሐፉን በሚገባ አንብበው በጭፍን ሳይሆን በገምቢ መልኩ የሚሰጡትን ማንኛውን ምአስተያየትና ሂስ ለመቀበል ዝግጁ መሆናቸውንም ኮ/ል ፍሰሃ በመግቢያው ላይ ገልጸዋል።

ጸሃይ አሳታሚ ድርጅት በኢትዮጵያ ጥንታዊ እና ዘመናዊ የፖለቲካ ታሪክ ጉዳዮች ላይ በርከት ያሉ መጽሃፍት እያሳተመ ለአንባብያን እያቀረበ ይገኛል። ይህም የታሪክ ቅርስን እየጣለልን የሚያልፍ ስራ ነው። ሊበረታታም ይገባዋል። እነሆ ዛሬም “አብዮቱና ትዝታዬ” ጀባ ብሎናል። ግንዛቤ ለመግኘት ያንብቡ – መጽሃፉ መተቸት ካለበትም ይተቹ። … በመጀመርያ ግን ያንብቡ! መልካም ንባብ!

የአርበኞች ግንቦት ሰባት አመራር አቶ ነዓምን ዘለቀ ለአድማጭ ጥያቄዎች የሰጡት መልስ-ክፍል 2-VOA Amharic

$
0
0

የአርበኞች ግንቦት ሰባት የዓለም አቀፍ አመራር የዉጭ ግንኙነት ሃላፊና የንቅናቄዉ ምክር ቤት አባል አቶ ነአምንን ዘለቀ በዝግጅቱ ላይ ለአድማጮች በሰጡት መልስ የአገር አድን ጥምረት ንቅናቄ የተፈጠዉ በኢትዮጵያ ስልጣን ለመያዝ ሳይሆን በስልጣን ላይ ያለዉን መንግስት አስወግዶ አገሪቱን ለዴሞክራሲያዊ አስተዳደር ለማመቻቸት ነዉ ብለዋል።

Ethiopia – Fitsum Gebretsadik – Lemiwedih Libe – (official music video) – New Ethiopian Music 2015

FC Barcelona vs UD Las Palmas 2-1 All Goals & Highlights (La Liga) 2015

$
0
0

The Argentina forward was withdrawn in the first half with what looked like a serious injury, before the in-form Uruguay striker took the game away from the visitors
Luis Suarez’s double helped Barcelona to a 2-1 win over Las Palmas in Saturday’s La Liga encounter at Camp Nou as Lionel Messi limped off with a knee injury.


የዩኒቨርስቲው በር ተሰብሯል! ዐምዶቹም ተነቃንቀዋል! –ዶ/ር ዳኛቸው አሰፋ (የቀድሞው የአ.አ ዩ የፍልስፍና መምህር)

$
0
0

በዚህ ጽሑፍ የማነሣቸው ርእሰ ጉዳዮች በአራት የተከፈሉ ናቸው፡፡ አንደኛው፡- ስለ ዩኒቨርስቲ አጠር ያለ መሠረታዊ ሐሳብ እና የአካዳሚያዊ ነጻነት መርሖዎች፤ ኹለተኛ፡- የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ በመንግሥት መዳፍ ሥር ስለ መውደቅ፤ ሦስተኛው፡- የፕሬዝዳንት ዶ/ር አድማሱ ጸጋዬን ገጸ ሰብእና (persona) በኹለት ወጎች ሥር ማብራራት ሲኾን፣ አራተኛው፡- የርእሰ ጉዳዮቹ ማጠቃለያ ነው፡፡

10959139_809531089095868_565801363633107881_n

(ሀ) ዩኒቨርስቲ እና አካዳሚያዊ ነጻነት
ከኹሉ አስቀድሞ አንባቢ ልብ እንዲልልኝ የምፈልገው፣ በዚህ ጽሑፍ የቀረቡት አስተያየቶች እና ምልከታዎች እንደ አንድ በፍልስፍና መስክ የተሰማራ ሰው መጠየቅ ያለባቸውን ነገሮች ለመጠየቅ ያለሙ ናቸው፡፡ ይህም ሐሳቦቹ እና ምልከታዎቹ በአጠቃላይ ተቀባይነት እንዲኖራቸው ከመከጀል ብቻ ሳይኾን ሳንጠይቃቸው ብናልፍ ትክክል አይኾንም ከሚል እምነት በመነሣት ነው፡፡
የዚህ ጽሑፍ አንደኛው ዓላማ የሚያጠነጥነው፣በዩኒቨርስቲ ምንነት ዙሪያ በመኾኑ ስለ ዩኒቨርስቲ ጠቅለል ያለ ዕሳቤ እና በተጨማሪም ዩኒቨርስቲን፣ “ዩኒቨርስቲ” የሚያሰኙትን ርእይ፣ ተልእኮ እና ግብ ማሳየት ነው፡፡
የዩኒቨርስቲ ዋነኛው ርእይ እና ተልእኮ፣ ዕውቀት ማፍለቅ ሲኾን፣ ያፈለቀውንም ለተማሪዎች ማስተላለፍ እና መተግበር ነው፡፡ ይህም ማለት የዩኒቨርስቲ ዋነኛው ተግባር ከዘመን ዘመን እየተሸጋገረ አኹን ላይ የደረሰውን ዕውቀት መጠበቅ እና መከባከብ እንዲኹም በተሟላ መልኩ ለትውልዱ ማሳወቅ እና ማስተላለፍ ነው፤ በተጨማሪም ከዚህ በፊት ያልነበረውን ሐሳብ እና ዕውቀት መፍጠርም ነው፡፡
ዩኒቨርስቲ የአንድ ሀገር ምሁራዊ ህልውና እና የሥልጣኔ ዕድገት መገለጫ በመኾኑ መንግሥታዊ ሥርዓቱ ከሌሎች ተቋማት በተሻለ የሕግ እና የነጻነት መብት ሊሰጠው ይገባል፡፡ እዚህ ላይ ትልቁ የጀርመን ፈላስፋ ካርል ያስፐርስ ስለ ዩኒቨርስቲ ምንነት ሲገልጹ፤ ዩኒቨርስቲ በመንግሥት ቁሳዊ እና ፋይናንሳዊ ድጎማ የሚተዳደር ቢኾንም ከሌሎች ተቋማት ለየት የሚያደርገው የራሱን ርእይ እና ተልእኮ ቀርጾ የሚተገብር እና የሚንቀሳቀስ አንጻራዊ ነጻነት ያለው በመኾኑ ነው፡፡ ለዚህም ነው፣ የዩኒቨርስቲ መምህራን የመንግሥት ደመወዝተኛ ቢኾኑም እንደ ሌሎቹ የመንግሥት ተቋማት ሠራተኞች (civil servants) የመንግሥትን ፖሊሲ ለማስፈጸም የተቀጠሩ አገልጋዮች የማይኾኑት፡፡
በተጨማሪም የዩኒቨርስቲ ዐቢይ ተልእኮ የምንለው፣ ተቋሙ እውነት ላይ ለመድረስ ማንኛውም ጉዳይ የሚጠየቅበት እና የሚመረመርበት ማእከል መኾኑ ነው፡፡ ይህንንም ተልእኮ በአግባቡ ለመወጣት ዩኒቨርስቲ በልዩ ልዩ ተቋማት ሥር ለሚያካሒደው ጥናት እና ምርምር ያልተገደበ ነጻነት እና መብት ይኖር ዘንድ ግድ ይላል፡፡ ዩኒቨርስቲ ነጻነቱን በማስቀደም ነው፣ የዕውቀት መዲና እና መፍለቂያ ኾኖ ከዘመን ዘመን እየተሸጋገረ የመጣው፡፡ የዩኒቨርስቲ ነጻነትን ባነሣን ቁጥር የአካዳሚያዊ ነጻነት ጥያቄ ቁልፍ የኾነ ድርሻ ያለው መሠረታዊ ሐሳብ እንደ ኾነ ግልጽ ነው፡፡
(ለ) አካዳሚያዊ ነጻነት
አካዳሚያዊ ነጻነት ማለት ማንኛውም መምህር በሥራ ገበታው ላይ ሊኖረው የሚገባውን ነጻነት እና መብት የሚደነግግ የሕግ መርሕ ነው፡፡ አኹን በዓለም ላይ በሰፊው ተቀባይነት ያገኙት የአካዳሚያዊ ነጻነት መርሖዎች፣ የዛሬ አንድ መቶ ዓመት ገደማ በአሜሪካን ሀገር በጉዳዩ ዙሪያ የጥናት ስብሰባ ከተደረገ በኋላ ተሳታፊዎቹ የሚከተሉትን አራት ነጥቦች አቅርበው፣ ሕጋዊ ከለላ ለማሰጠት በመቻላቸው እነሆ እስከ አኹን ድረስ ወሳኝ የኾኑ የአካዳሚያዊ ነጻነት መርሖዎች እና አዕማድ ኾነዋል፤ ፍሬ ሐሳቦቹም እንደሚከተለው ቀርበዋል፡፡
1. የመመራመር እና የማሳተም ነጻነት
ማንኛውም መምህር በፈለገው እና በመረጠው ርእስ ምርምር እና ጥናት የማካሔድ ሙሉ መብት አለው፡፡ በተጨማሪም በምርምር ያገኘውን ውጤት ያለምንም ዕንቅፋት እና ገደብ የማሳተም መብት አለው፡፡
2. መምህር በክፍል ውስጥ ስለሚኖረው ነጻነት
ማንኛውም መምህር ለሚያስተምረው ትምህርት ይኾናል የሚለውንና የሚበጀውን የማስተማርያ ጽሑፎችን የማካፈል እንዲኹም ማንኛውንም ትምህርት ነክ የኾኑ ጉዳዮችን በውይይት እና በጥያቄ ያለምንም ጫና ለተማሪዎቹ ሊያቀርብ ይችላል፡፡
3. በትምህርት ተቋም ቅጽር ውስጥ የሚኖር መብት/Intramural Right)
ማንኛውም መምህር አቅሙና ችሎታው እስከ ፈቀደ ድረስ የአንድን የዩኒቨርስቲ አስተዳደር እና አመራር ሳይፈራ እና ሳይሸማቀቅ የማሔስ እና የመተቸት ሙሉ መብት አለው፡፡
4. ከትምህርት ተቋሙ ቅጽር ውጭ ስላሉ ጉዳዮች የሚኖር መብት(Extramural Right)
ማንኛውም መምህር በሥራ ገበታው ላይ እያለ የሀገሩን የአስተዳደር፣ የፖለቲካ እና የማኅበራዊ ጉዳዮችን የመተቸት ሙሉ መብት አለው፡፡
እነዚህ ከላይ የተገለጹት መርሖዎች በሕግ ማህቀፍ ሥር መካተታቸው፣ በአካዳሚው ዓለም ውስጥ ለተሰማሩ መምህራን ሥራቸውን በአግባቡ እንዲያከናውኑና እንዲኹም ለወከባና ለእንግልት እንዳይዳረጉ መከታ ይኾናቸዋል፡፡
፪.
አዲስ አበባ ዩኒቨርስቲን ለመቆጣጠር የተደረገው ሒደት
ኢሕአዴግ ስለ ፖለቲካ ስትራቴጅና አቅጣጫ በ1997 ዓ.ም. ባወጣው ሰነድ ላይ፤ ስለ ሀገሪቱ ምሁራን የሚከተለውን ግምጋሜ አቅርቧል፡፡ ግምጋሜው የታየበትን መነጽር፣ ከዚህ በታች ስለምናቀርበው የዩኒቨርስቲው በመንግሥት ቁጥጥር ሥር መዋል መንደርደሪያ ይኾነናል፡፡
እንደ ኢሕአዴግ አመለካከት፣ምሁሩ ምንጊዜም ወደ ሥልጣን ማማተሩ ስለማይቀር በተቻለ መጠን የሥልጣን መወጣጫ መንገዱ ተዘግቶ መያዝ አለበት፡፡ ይህን ለማሳካት ምሁሩ የንዋይ ፍላጎቱ በተቻለ መጠን እንዲሟላለት ማድረግ አስፈላጊ ነው፡፡ በመኾኑም በሙያው ዙሪያ ባሉ ሳንካዎችና ጥቅማጥቅሞች ተጠምዶ ወደ ሀገራዊ ጥያቄዎች ሳይሻገር በእዚያው ማጥ እየዳከረ እንዲኖር ማድረግ ይኖርበታል፡፡
ከዛሬ ስድስት መቶ ዓመት በፊት፣ ታላቁ ኢትዮጵያዊ ሊቅ፣ ቅዱስ አባ ጊዮርጊስ ዘጋሥጫ፣ ከደረሷቸው መጻሕፍት መካከል ‘መጽሐፈ ምስጢር’ ብለው በሰየሙት ድርሳናቸው ውስጥ፣ ሳይማሩ እናስተምራለን ብለው ስለተነሡ የቤተ መንግሥት ባለሟሎች የሚከተለውን ብለው ነበር፡፡ ከአባ ጊዮርጊስ የወሰድነው ጥቅስ ሊቁ ለሌላ ጉዳይ የተናገሩት ቢኾንም ለያዝነው ርእስ የመንፈስ ቅርበት አለው ብለን ስለምናምን በዚሁ አገባብ የጠቀስነው መኾኑን ለአንባብያን እያስታወስን ጥቅሱን ያጎረሱንን መሪጌታ ሳናመሰግን አናልፍም፡፡
“እሉ እሙንቱ [መነኮሳት] እለ ቀዲሙ የዐየሉ ገዳመ አድባረ ወበዐታተ ወድኅረ ይትዋሐውሑ በአዕጻዳተ ነገሥት፡፡ ቀዲሙ ከመ ኢይትመሀሩ መጻሕፍተ ነቢያት ወሐዋርያት በንኡሶሙ ወጽኡ ገዳመ ወተግኅሡ እምዐጸደ ቤተ ክርስቲያን እንተ ይእቲ እመ ኩልነ ዘኢይነጽፍ ሐሊበ አጥባቲሃ፡፡ ወድኅረኒ ኢይፈጽም ገድሎሙ በጽማዌ ውስተ ገዳም ቦኡ ውስተ አብያተ ነገሥት ወበዊኦሙ ከመ ኢያርምሙ መሀሩ ዘኢትምህሩ ወሰበኩ ዘኢያእመሩ፡፡ ይልህቅኑ ሕፃን ዘእንበለ ሐሊበ አጥባተ እሙ ይሌቡኒ መነኮስ ዘኢተምህረ መጻሕፍተ ነቢያት ወሐዋርያት ከመ ይኩን መመህረ ለሰማዕያን ፡፡ ለሀወት ገዳም በኃጢአቶሙ ወለሀዋ አድባረ ምኔታት ወኢረኪቦቶሙ፡፡
“ለሀወት ቤተ ክርስቲያን በእንተ ዘነሠቱ አናቅጺሃ ነቢያተ ወነክነኩ አዕማዲሃ ሐዋርያተ፡፡ ወሠርዑ ሎሙ ሕገ ወሥርዓተ ዘኢይወጽአ እምእስትንፋሰ አፉሁ ለእግዚአብሔር ፡፡”
ትርጉም፡-
“እነዚህ [መነኮሳትም] ቀድሞ በበርሀ በተራሮችና በዋሻዎች የሚዘዋወሩ በኋላ ግን በነገሥታት ዐፀዶች ውስጥ የሚመላለሱ ናቸው፡፡ ቀድሞ በታናሽነታቸው ጊዜ የነቢያትና የሐዋርያትን መጻሕፍት እንዳይማሩ የጡቶቿ ወተት የማይደርቅ የኹላችን እናት ከኾነች ከቤተክርስቲያን ዐፀድ ርቀው ወደ ገዳም ወጡ፡፡ ኋላም ገድላቸውን በገዳም ውስጥ ኾነው በጭምትነት እንዳይፈጽሙ ወደ ነገሥታት ቤት ይገባሉ፤ገብተውም ዝም እንዳይሉ ለራሳቸው ያልተማሩትን ያስተምራሉ፤የማያውቁትንም ይሰብካሉ፣ሕጻን ያለ እናት ጡት ያድጋልን? መነኩሴስ ለሚሰሙ ሰዎች አስተማሪ ይኾን ዘንድ ያልተማረውን የነቢያትና የሐዋርያትን መጻሕፍት ያስተውላልን?
“ቤተ ክርስቲያን ስለ ኃጢአታቸው አለቀሰች፡፡ የገዳማት ተራሮችም እነርሱን ባለማግኘታቸው አለቀሱ፤ቤተ ክርስቲያን ነቢያት በሮቿን ስላፈረሱ፣ ምሰሶዎቿ ሐዋርያትንም ስለነቀነቁ አለቀሰች፡፡ ከእግዚአብሔር አንደበት ያልወጣውንም ሕግና ሥርዓት ለራሳቸው ሠሩ፡፡”
ከላይ በጥቅስ ከተቀመጠው የአባ ጊዮርጊስ ትዝብት የሚከተሉትን ፍሬ ነገሮች ነቅሰን ማውጣት እንችላለን፡፡ የአመራረጣችን መሠረት፣ ባለንበት ወቅት አንጋፋው የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ እንዴት ሙሉ በሙሉ በመንግሥት መዳፍ ሥር እንደ ወደቀ የጥቅሱ መንፈስ ማሳያ ኾኖ ስላገኘነው ነው፡፡ አኹን በሥልጣን ላይ ያለው ሥርዓት፣ ከገጠር ወደ ከተማ እንደ መጣው ኹሉ፣ የአባ ጊዮርጊስም ‘ምሁራን’ ከበረሓ ወደ ቤተ መንግሥት የመጡ በመኾናቸው ተመሳሳይነታቸው ከፍ ያለ ነው፡፡
የቅዱሱን ተግሣጽ በኹለት ምድብ በመክፈል በመጀመሪያ፣ የትዝብታቸውን መነሻ ቀጥለን ደግሞ፤ ድርጊቱ ያስከተለውን አሉታዊ ዉጤት እናያለን፡፡
ሀ. የትዝብታቸው መነሻ፡-
የተወሰኑ ምእመናን መንፈሳዊ ሕይወት በመፈለግ ወደ ዋሻ፣ አድባራት እና በረሓ ገቡ፡፡ መንፈሳዊ ተጋድሎ አልኾንላቸው ሲል በረሓውንና ዋሻውን ለቀው ወደ ቤተ መንግሥት ጠጋ አሉ፤ ወደ ቤተ መንግሥቱም አዘውትረው መመላለስ ጀመሩ፡፡ ከማዘውተራቸው ብዛት የቤተ መንግሥቱን አመኔታና ይኹንታ ተቀዳጁ፡፡ የሹማምንቱን ቅቡልነት ቢያገኙም በየበረሓው ወጣትነታቸውን በከንቱ አባክነው በዘመኑ ከቤተ ክርስቲያን ብቻ ይገኝ የነበረውን ትምህርት ሳያገኙ ስለቀሩ፣ የቤተ መንግሥት ባለሟልነታቸውን ተጠቅመው፣ ያልተማረውን ምእመን እናስተምራለን ብለው ተነሡ፡፡
ለ. ድርጊቱ ያስከተለው አሉታዊ ውጤት፡-
አባ ጊዮርጊስ ዘጋሥጫ፤ኹኔታው ያስከተለውን አሉታዊ ውጤት በኹለት ዘይቤ (Metaphor) ያስረዳሉ፡፡ እነዚህም፡- “በሮቿ ተሰበሩ” እና “አዕማዷ ተነቃነቁ” የሚሉት ናቸው፡፡
በሮቿ ተሰበሩ፡-
“በሮቿ ተሰበሩ” ከሚለው ዘይቤ ውስጥ በዛ ያሉ ምልከታዎችን መንቀስ ይቻላል፡፡ በር ስንል የሚፈለገው የሚገባበት፣ መግባት የሌለበትን ደግሞ መቆጣጠሪያ ሥርዓት መኾኑን ነው የሚያመለክተው፡፡ በመኾኑም የተናጋና የተሰበረ በር ያለው ተቋም፤ ማንም እንዳሻው የሚገባበትና የሚወጣበት፣ ሥርዓት አልባ ጎዳና ኾኗል ማለት ነው፡፡ ቤተ ክርስቲያን የራሷን ልዕልና አስጠብቃ መዝለቅ ተስኗታል እንደማለትም ነው፡፡
አዕማዷ ተነቃነቁ፡-
የአንድ ቤት ዐምዱ ወይም ምሶሶው ከተነቃነቀ፣ጨርሶ የመፈራረሱ ጉዳይ ተቃርቧል ማለት ነው፡፡ በአባ ጊዮርጊስ ዕይታ፤ የቤተ ክርስቲያኒቷ ዶግማ፣ ቀኖና፣ ትውፊት በአጠቃላይ አስተምህሮዋ ተናግቷል ማለታቸውን ያሳያል፡፡ በተፈጠረው አግባብ የለሽ አካሔድና ቀውስ የቤተ ክርስቲያኒቷ አበው አዘኑ፤ አለቀሱም፡፡
ወደ ጥንተ ነገራችን ስንመለስ፤የአባ ጊዮርጊስ ዘጋሥጫ አቀራረብ፣ አኹን በዩኒቨርስቲው ቅጥር ውስጥ የሚካሔደውን ኹኔታ በሚገባ ለመረዳት እንደ መነጽር ይኾነናል፡፡ ከኹሉ አስቀድሞ፣ የአባ ጊዮርጊስ ‘መምህራን’ እናስተምራለን ብለው የተነሡት ራሳቸው ሳይማሩ ያልተማሩትን ሰዎች ለማስተማር ነው፡፡ በእኒህ ኹለት ዓመታት ውስጥ፣ በዩኒቨርስቲው ግቢ ውስጥ እናሠልጥን ብለው የተነሡት የመንግሥት ሹመኞች ራሳቸው በሚገባ ሳይማሩ፣ አልተማሩም የሚሏቸውን ሳይኾን፣ የተማሩትን ክፍል ለማስተማር መነሣታቸው ነው፡፡ ከዚኽ አንጻር አባ ጊዮርጊስ የታዘቧቸው መምህራን ከአኹኖቹ እናስተምር ባዮች በእጅጉ የተሻሉ ኾነው እናገኛቸዋለን፡፡ ይኸውም የቀድሞዎቹ፣ ራሳቸው ባይማሩም እናስተምር ያሉት ያልተማሩትን ሲኾን የእኛዎቹ ግን እናስተምር ብለው የተነሡት የተማሩትን በመኾኑ ነው፡፡ አባ ጊዮርጊስ በዚህ ዘመን ቢኖሩ ኀዘናቸው ምን ያኽል በበረታ ነበር!!
አባ ጊዮርጊስን በእጅጉ ያሳዘናቸውና ያስገረማቸው፣ ቤተ መንግሥት በፍጥረቷ የአስተዳደር መንገድ መቀየስ እንጂ የዕውቀት ምንጭ ወይም የምሁርነት ምኩራብ ሳትኾን፣ ዐዋቂዎች ነንና እናስተምር እያሉ የሚነሡባት ማእከል ኾና ስላገኟት ነው፡፡ አኹን ወዳለንበትም ጊዜ ስንመጣ፣ ብዙዎችን እያሳሰበ ያለው በየዩኒቨርስቲው እናሠልጥን እያሉ የሚመጡት ሰዎች አኳኋን ነው፡፡ ልክ እንደ አባ ጊዮርጊስ ‘ምሁራን’ አስቀድመው ወደ በረሓ ከወጡ በኋላ ተመልሰው ቤተ መንግሥቱን በቁጥጥራቸው ሥር አዋሉ፡፡ ከዚያም ቤተ መንግሥቱም ዩኒቨርስቲውም አይቅርብን ብለው የዩኒቨርስቲውን መምህራን እናስተምራለን ብለው ብቅ አሉ፡፡
የአባ ጊዮርጊስ ኀዘን የበረታው፣ እኒኽ ‘ምሁራን’ ቤተ ክርስቲያን እንደ በሮቿ የምታያቸውን የነቢያት አስተምህሮ ስለሰበሩና በምሰሶ የተመሰሉትን የሐዋርያትን ዶግማና ቀኖና ስላነቃነቁ ነው፡፡ ብዙዎችን ታዛቢዎች በእጅጉ እያሳሰባቸው ያለው በአስተማሪነትና በአሠልጣኝነት ስም፤ ዩኒቨርስቲው የዕውቀት፣ የጥበብ፣ የምርምርና የመሳሰሉት ዕሴቶች ገዳም ኾኖ ሳለ፤ ሊቃነ ማእምራኑ (ፕሮፌሰሮቹ) ያስቀመጧቸውን ሚዛኖች (በሮች) በመስበር አዕማዷን ስላነቃነቁት ነው፡፡የቤተ ክህነቱ በር እንደተሰበረው ኹሉ፣ የየኒቨርሲቲውም በር ተሰብሯል ስንል ዩኒቨርስቲው ተማሪዎቹንም ኾነ መምህራኑን መርጦ የመቀበል መብቱ ተገፍፎ፣ በፖለቲካ ትእዛዝ እንዲሞላ በመደረጉ፣ ማንም እንዳሻው የሚገባበትና የሚወጣበት ኾኗል ማለታችን ነው፡፡ የአዕማዷን መነቃነቅ በምናነሣበት ጊዜ በዋናነት የምናቀርበው፣ ዩኒቨርስቲው የነበረው የማስተማር ሥነ ዘዴ ተሽሮ፣ ከፖለቲካ ኃይሉ በመጣ ማዘዣ፣ እነርሱ ይበጃል የሚሉትን አካሔድ ተግባራዊ እንዲያደርግ መገደዱን ነው፡፡ ለዚህም ማሳያ የሚኾነው፣ ከቢፒአር እስከ ቢኤስሲ እና አንድ ለአምስት አደረጃጀትን መምህራኑ ሳይመክሩና ሳይዘክሩበት፣ ዩኒቨርስቲው እንዲከተል መደረጉ ነው፡፡ የአባ ጊዮርጊስ ‘ምሁራን’፣ የመንግሥትን ኃይልና ቤተ ክርስቲያንን ገና በሚገባ ያልተቆጣጠሩ ሲኾን፣ የአኹኖቹ ምሁሮች ግን ሥልጣንን ሙሉ በሙሉ ለያዙ ኃይሎች ተጠሪዎች ናቸው፡፡ በመኾኑም ከንኡሳን (ደቃቂን) ሓላፊዎች እስከ ዐቢይ አለቃው – ፕሬዝዳንቱ፣ ድረስ ለቤተ መንግሥቱ የፖለቲካ ቀኖና ተገዥና ተኣማኒ በኾኑ እሺ ባዮች እንዲያዝ ተደርጓል፡፡
እውነተኛ ዩኒቨርስቲያዊ ይትበሃል ተሽሮ፣ የበረሓ ጀግኖች እንዳፈተታቸው የሚናኙበት ኾነ፡፡ የመማር ማስተማር ሒደቱንም፣ ዩኒቨርስቲያዊ ልዕልናው ስለ ተገፈፈ ሳይንሳዊና ሞያዊ አሠራሩ ተሻረ፡፡ በቦታውም ከፖለቲካው ጽሕፈት ቤት በሚመነጭ ኢሕአዴጋዊ ትእዛዝ በሩን አፈረሱት፤ ዐምዱንም አነቃነቁት፡፡ ካርል ያስፐርስ የገለጹት ‘አማናዊው ዩኒቨርስቲ’ እና እውነተኞቹ ምሁሮቿ ስለ እነዚህ ሰዎች አድራጎት አብዝተው ያዝናሉ፡፡ የቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ዩኒቨርስቲ ኮሌጅ ሲቋቋም፣ ሊቁ ዶክተር እጓለ ገብረ ዮሐንስ፣ የበሩን ኹለት አዕማድ ‘በዕውቀት’ እና ‘በሠናይ’ (Virtue) በመመሰል የዘመሩለት፣ ማንም ሰው ሊያየው በሚችለው መልኩ መሠረቱ ተናጋ፤ ውድቀቱም ተቃረበ፡፡

Tottenham Hotspur vs Manchester City 4 -1 All Goals HD Premier League 2015

$
0
0

Goals from Eric Dier, Toby Alderweireld, Harry Kane and Erik Lamela ensured a controversial win over the Premier League table toppers
Harry Kane ended his long wait for a Tottenham goal as his side came from 1-0 down to thrash Manchester City 4-1 at White Hart Lane on Saturday.

Betoch Special Program – Remembering Actress Seble Tefera

$
0
0

Betoch Special Program – Remembering Actress Seble Tefera….የቤቶች ተከታታይ ድራማ ተዋንያን በመኪና አደጋ ህይወቷ ያለፈው አርቲስት ሰብለ ተፈራን በተመለከተ ያዘጋጁትን ዝግጅት ሊንኩን ተጭነው ይመልከቱ።

Mainz vs Bayern Munchen 0-3 Full Highlights HD ~ Bundesliga 26/9/2015

$
0
0

The striker made it seven goals in a week with a double on Saturday, while Kingsley Coman also found the back of the net after scoring his first goal for the club last weekend
Robert Lewandowski reached a century of Bundesliga goals to help Bayern Munich secure their best start to a league season by comfortably beating Mainz 3-0 at the Coface Arena.

ድምጻዊት ዘውዲ ለመጀመርያ ግዜ ወደኢትዮጵያ ልትሄድ ነው

$
0
0

በእናቷ ኢትዮጵያዊ በአባቷ ኤርትራዊ የሆነችው ድምጻዊት ዘውዲ ሓብቲ አወሎም ለመጀመርያ ግዜ ወደኢትዮጵያ ልትሄድ ነው።
ከልጅነቷ የጀመረው ሙዚቀኛ የመሆን ፍላጎቷ ድምጻዊ በሆነው አባቷ እገዛ ዛሬ የደረሰችበት ደረጃ የደረሰችው ዘውዲ የተወለደችው ኒውዮርክ ሲሆን ያደገችው ኒውጀርሲ ነው።
በዩቲዮብ ሙዚቃዋ ከ16ሚሊዮን በላይ በሚሆኑ ተመልካቾች የታየላት ሲሆን የራሷን ሙዚቃዎች በተለያዩ ቦታዎች ከማቅረቧም ሌላ ከታዋቂ ድምጻዊያን ጀርባ ተቀባይ ድምጻዊ ሆና ሰርታለች ።የ23 ዓመቷ ዘውዲ የእናት አገሯ ኢትዮጵያን ለመጀመሪያ ግዜ ለማየት ጉዞ መጀመሯ ልዩ ስሜት እንደተሰማት ገልጻለች ።ከሙዚቃዎቿ አንዱ የሆነውን በአማርኛና በእንግሊዝኛ የተጫወተችውን “into the night “እንጋብዛችሁ።

Viewing all 3774 articles
Browse latest View live