Quantcast
Channel: Kalkidantube
Viewing all 3774 articles
Browse latest View live

የኢትዮጵያ አየር መንገድ አውሮፕላንን የጠለፈው ረዳት ፓይለት መኪና ለጨረታ ቀረበች

$
0
0

በጥር 2006 ዓ.ም. ከአዲስ አበባ ወደ ሮም ጣሊያን ሲበር የነበረውን የኢትዮጵያ አየር መንገድ ቦይንግ 767 አውሮፕላን ጠልፎ ጄኔቫ ስዊዘርላንድ ያሳረፈው ረዳት አብራሪ ኃይለ መድኅን አበራ ንብረት የሆነች የቤት መኪና በሐራጅ ለጨረታ ቀረበች፡፡
66db0da56aa2ffdb291f9af3242f4601_L

የሰሌዳ ቁጥር አአ 2-A32521 መኪና ጨረታ ያቀረበው ዘመን ባንክ ነው፡፡ ረዳት አብራሪው ለመኪና ግዢ ከዘመን ባንክ የተበደረው ብድር ስላልተከፈለው ባንኩ ተሽከርካሪዋን በጨረታ ለመሸጥ መገደዱን አስታውቋል፡፡

ባንኩ ተሽከርካሪዋን ለጨረታ ያቀረበው በሐራጅ መነሻ ዋጋ ብር 261,503.37 ነው፡፡ ጨረታው የሚካሄደው በመስከረም ወር 2008 ዓ.ም. ነው፡፡ ረዳት አብራሪ ኃይለ መድኅን መኪናዋን የገዛው ከአውሮፕላን መጥለፉ ጥቂት ወራት ቀደም ብሎ እንደነበር ለማወቅ ተችሏል፡፡

ኃይለ መድኅን ስዊዘርላንድ ውስጥ የፖለቲካ ጥገኝነት ቢጠይቅም የአገሪቱ ፖሊስ በቁጥጥር ሥር አውሎት ፍርድ ቤት አንድ ጊዜ የቀረበ ሲሆን፣ ከዚያ በኋላ ጉዳዩ በምን ደረጃ ላይ እንዳለ አይታወቅም፡፡ ለስዊዘርላንድ ኢሚግሬሽን ባለሥልጣን በተደጋጋሚ ጥያቄ ቢቀርብም ምላሽ ለመስጠት ፈቃደኛ ሳይሆን ቀርቷል፡፡

ኢትዮጵያ ውስጥ የፌዴራል ዓቃቤ ሕግ በግለሰቡ ላይ ክስ መሥርቶ፣ የፌዴራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት በሌለበት 19 ዓመት ፅኑ እስራት እንደተፈረደበት ይታወሳል፡፡
ምንጭ ሪፖርተር ጋዜጣ


መስከረም 03/2004 ዓ.ምን ሳስታውሳት… አንዷለም -ወ- እስክንድር -(ኤልያስ ገብሩ)

$
0
0

መስከረም 03 ቀን 2004 ዓ.ም እኔና ጓደኛዬ አናንያ ሶሪ በወቅቱ እንሰራባት ለነበረው አውራምባ ታይምስ ጋዜጣ፣ በከፍተኛ ትምህርት ጉዳይ ዙሪያ ፊቸር ጽሑፍ በጋራ ለማዘጋጀት አቅደን፤ ለመረጃ ግብዓት መቅረፀ ድምጻችንን ይዘን በቀድሞ አንድነት ለፍትህና ለዴሞክራሲ ፓርቲ ቢሮ በጥዋት ደረስን፡፡ ለተወሰኑ ጥያቄዎቻችን መረጃ እንዲሰጡን ቀድመን ጥያቄ በማቅረብ ቀጠሮ ይዘን የነበረው ከአቶ አስራት ጣሴ ጋር ነበር፡፡ እሳቸውም ከቀጠሯችን ቀደም ብለው በቢሯቸው ተገኝተዋል፡፡ ከሰላምታ ቀጥለን ወደዋናው ጉዳያችን ዘለቅን፡፡ በዚህ መካከል የፓርቲው ሊቀመንበር ዶ/ር ነጋሶ ጊዳዳ፣ የፓርቲው ፀሐፊ አቶ አንዷለም አራጌና በአሁን ወቅት የዘነጋሁት አንድ ሰው አቶ አስራት ቢሮ ድረስ በሩን በማንኳኳት ገቡ፡፡

12002823_885053151580709_1952369173699994291_n
ከሰዓት ከሁሉም ጋር ሰላምታ ተሰጣጠን፡፡ የእነአንዷለም አመጣጥ አቶ አስራትን ጠርተው አጠር ያለች ኢ-መደበኛ ስብሰባ ለማድረግ ያለመ መሆኑን ከንግግራቸው ተረድተናል፡፡ ‹‹አስቸኳይ ነው›› ስለተባለ አቶ አስራት እኛን ይቅርታ በመጠየቅ ቀጠሯችንን ከሰዓት በኋላ ማድረግ እንችል እንደሆነ በትህትና ጠየቁን፡፡ እኔ እና አናንያም ሁኔታውን በመረዳት 10፡00 ሰዓት ላይ በድጋሚ ቀጠሮ ይዘን ወጣን፡፡ በወቅቱም አንዷለም አንድ ቀልድ ፈገግ እያለ በመናገር አስቆን እንደነበረም አስታውሳለሁ፡፡
እኔና አናንያም ጊዜውን ለመጠቀም በሚል፣ ሽሮሜዳ አሜሪካ ኤምባሲ ፊት ለፊት ወደሚገኘውና በዶ/ር ተስፋዬ ተሾመ ዋና ዳይሬክተርነት ወደሚመራው የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት አግባብነትና የጥራት ኤጀንሲ (Higher Education Relevance and Quality Agency) መ/ቤት በመሄድ ከህዝብ ግንኙነት ባለሙያው የምንፈልገውን የሰነድ እና የድምጽ መረጃ አገኘን፡፡ ከቀጠሯችን ቀደም ብለንም አቶ አስራት ቢሮ ደረስን፡፡ የአቶ አስራት ፊት ግን ጥዋት እንዳየነው አልነበረም፡፡ ደስ የማይል ስሜት አረብቦባቸዋል፡፡ ‹‹አንዷለምን እኮ ፖሊሶች አሁን ወሰዱት›› ብለው የሚያውቁትን ያህል ዘርዝረው ነበሩን፡፡ ‹‹ጥዋት ህጻን ልጁ ለመጀመሪያ ጊዜ ት/ቤት ገብቶለት ከሰዓት በኋላ ደስ ብሎት ከት/ቤት ሊያመጣው አቅዶ እንደነበረ ነግሮኝ፣ በጣም ያሳዝናል›› አሉ፡፡ እኛም በአቶ አስራት ቢሮ በጋራ አዘንን፡፡ በዚህ ደስ በማይልና ባልተረጋጋ ስሜት ውስጥ ቃለ-መጠይቁን ማድረግ በድጋሚ ሳንችል ቀረንና ከፓርቲው ቅጥር ግቢ ወጣን፡፡ ከቢሮው ጀምሮ እስከዋናው አስፋልት ድረስ ፊታቸውን ከስክሰው፣ ፈንጥር ፈንጠር ብለው በመቆም አካባቢውን በአይነ ቁራኛ የሚመለከቱ፣ በእኔ አጠራር ‹‹ተከታትሎ አደሮች›› ነበሩ፡፡ በዋናው የአራት ኪሎ መገናኛ መንገድ ዳር በሚገኘው ‹‹ፍሮስቲ ባርና ሬስቶራንት›› መግቢያ በር ጋር ቆሞ ከፓርቲው ቢሮ መውጣታችንን ያወቀው አንድ ጠቆር ያለ ‹‹ተከታትሎ አደር›› አፈጠጠብን፤ እኛም አፍጥጠን አጸፋውን መለስንለት፡፡ እርሱም ወዲያው አንገቱን ለማቀርቀር ጥረት አደረገ፡፡ [ብዙ ጊዜ እንደዚህ አይነት ሰዎች ይገርሙኛል፤ ልባቸው በፍርሃት ውስጥ ሆኖ፣ ሰው እንዲፈራቸው የሚያደርጉት የደካማ ሥነ-ልቦና የትግበራ ሙከራቸው በጣም ያናድደኛል]
የእኔና አናንያ ቢሮ እዚያው ቤል-ኤር አከባቢ ስለነበረ ወዲያው ገባን፡፡ ሁሉም የጋዜጣዋ ባልደረቦች እስሩን ሰምተዋል፡፡ አቤል ዓለማየሁ፣ በዚሁ ቀን፤ ቀትር ላይ የዛሚዋን ሚሚ ስብሐቱ ‹‹እነአንዷለም ይታሰሩ›› የሚል ይዘት ያለው ‹‹የእስር ዋረንት›› ዘመቻዋን ካደመጠ በኋላ ከሰዓታት በፊት ለአንዷለም ስልክ ደውሎለት እንደነበረ በቁጭት ሲናገር አደመጥነው፡፡ የጋዜጠኛ እስክንድር ነጋን መታሰርም በዚሁ ቢሮ ውስጥ ተረዳን፡፡ ሀዘን …ዝምታ …ቁጭት …ድጋሚ የሀዘን ስሜት ….ተፈራረቁ፡፡
የጋዜጣዋ ባልደረቦች፣ ኢ-መደበኛ ኤዲቶሪያል ስብሰባ አድርገን፣ በቀጣይ ዕትም ላይ ንጹሕ ወገኖቻችንን ዋጋ እያስከፈለ ስለሚገኘው የጸረ-ሽብርተኝነት አዋጅ ፊቸር ጽሑፉ እንዲደረግ ተስማማን፣ በቅዳሜ ዕትምም ተደረገ፡፡ ምሽት በሁለት ሰዓት ላይ፣ በቀድሞ የኢቴቪ ዜና እወጃ የአንዷለምንና የእስክንድርን የእስር ሁኔታ በፎቶ ግራፍ ተደግፎ ተመለከትን፡፡ ….
በነሐሴ ወር 2003 ዓ.ም መጨረሻ አካባቢ ከጋዜጠኛ እስክንድር ነጋ ጋር የወቅቱን የዓረብ ሀገራት አብዮት አስመልክቶ ሙያዊ ትንታኔ እንዲሰጠን እና ከዚህም አኳያ የሀገራችንን ነባራዊ ሁኔታ በእርሱ አተያይ ምን እንደሚመስልና ተያያዥ ሀገራዊ ጥያቄዎችን በማንሳት ከእኔ ጋር ሰፊ ቃለ ምልልስ አደርግን – በአራት ኪሎ ቱሪስት ሆቴል፡፡

12011337_885053174914040_8644077110975029211_n
እስክንድርን ቃለ-መጠይቅ እያደረኩለት ባለሁበት ወቅት፣ በዓለም ሀገራት ላይ ስለተደረጉ አብዮቶች አነሳስና ውልደት ታሪካዊ የዓ.ም ፍሰታቸውን ሳያዛንፍ ሲተነትን መስማቴ አስደምሞኝ ነበር፡፡ ቃለ-ምልልሱ አልቆ ቢሮ ገባሁና ወደወረቀት ላይ ልገለብጠው ስል የቃለ ምልልሱ ድምጽ የለም፡፡ በጣም ግራ ተጋባሁ፣ ከባልደረቦቼ ጋር ደጋመን ሞከርነው ግን ምንም የእስክንድር ድምጽ የለም፡፡ ለካ በስህተት ከባልደረባዬ ናፍቆት ዮሴፍ ጋር የማይሰራ መቅረፀ-ድምጽ መቀያየሬን ዘንግቼው ነበር፡፡ በጣም ተናደድኩ – መሰል ነገር በጋዜጠኝነት ሕይወት የሚገጥም ነገር መሆኑን ባውቅም፡፡ ከቢሮ ወጥቼ ተረጋግቼ አሰብኩ፡፡ ያን የመሰለ ቃለ-ምልልስ መቅረት የለበትምና በድፍረት ለእስክንድር እውነቱን ልነግረው ወስኜ ፡፡ ጥቂት የማይባሉ ሰዎች ቃለ-ምልልስ ካደረጉ በኋላ ድንገት መሰል ነገር መፈጠሩ ሲነገራቸው በጣም ይናደዳሉ፤ በድጋሚ ቃላቸውን ለመስጠት ፍቃደኛም ላይሆኑ እንደሚችሉ አውቃለሁ፡፡ እስክንድር ግን በጣም በሚገርም ደወልኩለትሁኔታ ሁኔታውን ተረድቶ በትህትና ‹‹መቼ ይመችሃል›› አለኝ፡፡ በጣም ደስ ብሎኝ በነጋታው ከሰዓት በኋላ እዚያው ቱሪስት ሆቴል ተቀጣጠርን፡፡
ቃለ-ምልልሱን ከመጀመራችን በፊት ወደእኔ ጠጋ አለና ‹‹ከጀርባህ ደህንነቶች አሉ፤ እነሱ መኖራቸውን ሳታስብ ጥያቄህን ጠይቀኝ›› አለኝ፡፡ ዞሬ አየኋቸው፤ ሁለት ናቸው፡፡ ሁለመናቸው እኛ ጋር ነው፤ እየታወቁም ፍጥጥ ብለው ሲያዩና ጆሯቸውን ሲቀርሱ ምንም እፍረት አይነበብባቸውም፡፡
ቃለ-ምልልሱ ሲጀመር ግን ረሳኋቸው፤ የእስክንድር ተመስጧዊ ትንታኔ ብዙ ነገር ያስረሳ ነበር፡፡ በመጨረሻም ደስ የሚል ቃለ-ምልልስ ከእስክንድር ጋር አደረግን፡፡ ‹‹በግሌ፣ ትንታኔህ በጣም ማርኮኛል፤ ከአንተ ጋር አንድ ቀን ተገናኝተን ካንተ ብዙ መማር የምፈልጋቸው ነገሮች አሉኝ›› አልኩት፡፡ ‹‹ኤልያስ እኔ ራሴ ካንተ ብዙ ነገር መማር እፈልጋለሁ፤ ደስ ይለኛል፤ ከአዲስ ዓመት በኋላ እንገናኛለን›› አለኝ በሚያስገርም ትህትና፡፡
መስከረም 02 ቀን 2004 ዓ.ም ለእስክንድር ደወልኩለት፡፡ ለመስከረም 05 ቀን ልንገናኝ ቀጠሮ ያዝን፡፡ ‹‹እንዲያውም አንተ ከፌዴራል የሥነ-ምግባርና የፀረ-ሙስና ኮሚሽን ኮሚሽነር አቶ አሊ ሱሌይማን ጋር ያደረከውን ሰፊ ቃለ-ምልልስ አንብቤ በአንድ ጉዳይ ላይ ጽሑፍ አዘጋጅቻለሁ፡፡ በባለፈው ዕትም ቃለ-ምልልሴ ስለወጣ ጋዜጣው ላይ በተደጋጋሚ ቦታ እንዳልይዝ ለቀጣይ እትም አደርሳለሁ›› አለኝ፡፡
ለኮሚሽነር አሊ ‹‹አንድ ዓለም አቀፍ ተቋም ከኢትዮጵያ የተመዘበረ 8.4 ቢሊየን ዶላር ገንዘብ ከውጪ ባንክ መገኘቱን ይፋ አድርጓል፡፡ ስለዚህ ምን ምላሽ አለዎት? …ብሩ በኢትዮጵያ አቅም በቃላሉ የሚታይ ነው እንዴ?!›› የሚሉ ተከታታይ ጥያቄዎችን አቅርቤላቸው ነበር፡፡ ኮሚሽነሩም ‹‹ግድ የለህም …ይ…ሄ…ን…ን ከጥያቄህ ብታወጣ? ሌላ ዓላማ ስላለው ነው፡፡ ከሕገ-ወጥ የገንዘብ ዝውውር (Money Laundry) ጋር አብሮ ተያይዞ የሚመጣ ነገር አለ፡፡ ለእናንተ ለሚዲያ የማይጠቅም ነገር ነው፡፡›› በማለትና ተጨማሪ ነገር መግለጽ ሳይፈልጉ የተዳፈነና የተድበሰበሰ መልስ ሰጥተውኝ ነበር፡፡ እስክንድር እንደነገረኝ ከሆነም፣ ከዚህ ጥያቄና መልስ በመነሳት፣ ይህ የተመዘበረ ገንዘብን በተመለከተ እና ኮሚሽነር አሊ ይህህን አስመልክቶ ለምን ለመመለስ እንደከበዳቸው የራሱን ምልከታ ለመግለጽ ነበር ጽሑፉን ያዘጋጀው፡፡ ግን ምን ያደርጋል በቀጠሯችን መሰረት ከእስክንድር ጋር ተገናንተን ሳንወያይ እና ጋዜጣዋ ላይ ሙስናን አስመልክቶ እንዲታተም ያዘጋጀውን ጽሑፍ ሳይሰጠኝ ነበር ልክ የዛሬ አራት ዓመት የበኩር ልጁን ከት/ቤት አውጥቶ ወደቤታቸው ሊሄዱ ሲሉ ነበር በግፍ በፖሊሶች የተያዘው! ልክ የዛሬ አራት ዓመት ነበር፣ ውድ ልጁን ከእጁ መንጭቀው በህጻን ልጁ ፊት የብረት ካቴና ያጠለቁለት! የአብራኩ ክፋይ የሆነው ናፍቆት እያለቀሰ ነበር ይዘውት ወደቤቱ ለብርበራ ያመሩት፡፡ አንዷለምም ቢሆን ት/ቤት ለመጀመሪያ ጊዜ የገባለትን ልጁን እንደአባት ከትምህርት ቤት በደስታ ሊያወጣው እንደናፈቀ ነበር ወደማዕከላዊ የተላከው፡፡
እንግዲህ እንዲህ ነች ኢትዮጵያ ሀገራችን!!!
…..እናንተ የህሊና እስረኞች፡- አንድ ቀን ከእስር የምትፈቱበትንና ከውድ ቤተሰቦቻችሁ እና ከኢትዮጵያ ህዝብ ጋር የምትገናኙበትን ቀን እሻለሁ!!!
በእስራችሁ ሳቢያ ከባድ ዋጋን በመክፈል ላይ ለሚገኙት ውድ ቤተሰቦቻችሁም በሙሉ፣ ፈጣሪ ይበልጥ ውስጣዊ ጥንካሬን ይስጣቸው፤ ተስፈኛም ሁኑ እላለሁ!!!

The last moments of the late SEBLE TEFERA.-ALEMNEH WASSE NEWS)

$
0
0

The last moments of the late SEBLE TEFERA…………The last moments of the late SEBLE TEFERA……The last moments of the late SEBLE TEFERA….The last moments of the late SEBLE TEFERA.

How President Obama won a 2nd Nobel Peace Prize on social media

$
0
0

This past weekend, many people who follow Facebook news threads were fooled regarding a very believable story about President Barack Obama. The news feed had origins from websites with names such as National Report.net, DailyNewsBin, Abcnews.com.co, USAtoday.com.co and even MSNBC.com.co. The problem is all of these websites are fake news sites designed with story titles to fool the reader.

obama1
The story title this time was “Obama to receive second Nobel Peace Prize” and despite the wishes and fears of many, it is false. There has been no announcement from the Nobel Prize committee located in Oslo, Norway, about President Obama or any of the possible nominees for the 2015 Nobel Peace Prize. This is in keeping with the organization’s secrecy rule, and according to its official website, “The Committee does not itself announce the names of nominees, neither to the media nor to the candidates themselves.”

This year there are 273 candidates for the Nobel Peace Prize; 68 organizations and 205 individuals. The official announcement date for the winner will be Friday, Oct. 9, 2015, at 11 a.m.

There are no laws that punish fake news websites that spread these rumors due in part to disclaimers that appear labeling their stories as satire. But for those looking for fast, up-to-date news, it is easy to be fooled by these websites. In some cases, clicking on the website link can load your computer or smartphone with cookies or a virus that can steal information or flood the user with unwanted pop-up ads. So as a rule, be wary of stories that seem too good to be true and check your sources before you spread a fake story on social media.
http://rollingout.com/

ምኞትና ተግባር ምንና ምን ናቸው? (ርዕዮት አለሙ)

$
0
0

በአዲሱ አመት ዋዜማ የፖለቲካ እስረኞችን ለመጠየቅ ወደ ቂሊንጦ እስርቤት ከእህቴ ጋር ሄጄ ነበር፡፡ ስማችንን እና የምንጠይቃቸዉን እስረኞች ስም ካስመዘገብን በኋላ መታወቂያችን አሳይተን ወደዉስጥ ልንገባ ስንል መታወቂያዉን የምትመለከተዉ ፖሊስ ስማችንን ካነበበች በኋላ “ቆይ ቆይ የእናንተማ መጠየቅ አለበት” አለችንና መታወቂያችንን ይዛ ከበር መለሰችን፡፡ ከበሩ አጠገብ በሚገኝ ጎብኝዎች ወረፋ በሚጠብቁበት የእንጨት መቀመጫ ላይ አረፍ እንዳልን በሃሳብ ላይ ታቹን ማለት ጀመርኩ፡፡

1959250_629681597105784_1036270970_n
እንድንገባ ይፈቅዱልን ይሆን ወይስ የቃሊቲዎቹ እንዳደረጉት “ፍቃድ የላችሁም” የሚል አስቂኝና አናዳጅ መልስ በመስጠት ይመልሱን ይሆን? ለሚለዉ ጥያቄ መልሱ እኔዉ ጋር ያለ ይመስል አጎንብሼ ማሰቤን ቀጠልኩ፡፡ ቀና ስል ከፊት ለፊቴ “ማረሚያ ቤቱ” ለእስረኛ ቤተሰቦች መልካም ምኞቱን የገለፀበት ወረቀት ተለጥፎ ተመለከትኩ፡፡ ከአራት አመታት በላይ በመኖር የእስርቤቶቹን አሰራር አዉቀዋለሁና ተመሳሳይ የመልካም ምኞት መግለጫ የያዘ ወረቀት ለእስረኛዉም ተለጥፎ እንደሚሆን አልተጠራጠርኩም፡፡
ሰላም እየነሳ ሰላም “የሚመኝ”፣ ህክምና እየከለከለ ጤንነትን “የሚመኝ”፣ የሚዋደዱ ሰዎችን ከሽቦ ወዲያና ወዲህ ሆነዉ እንኳን እንዳይተያዩ እየከለከለ ፍቅርን “የሚመኝ” . . .ተቋም ! አንድ ፖሊስ ወደኛ እየቀረበ ሲመጣ ሀሳቤ ተቋረጠ፡፡ መታወቂያዬን እየመለሰልኝ መግባት እንደማልችል ነገረኝ በኋላ ለእህቴም ተቀራራቢ መልስ በመስጠት መታወቂያዋን መለሰላት፡፡ ለምን ለሚለዉ ጥያቄያችን “አላዉቅም፡፡ የተወሰነውን ንገር ተብዬ ነው” የሚል ምላሽ ሰጠን፡፡ ምን አይነት አምባገነንነት ነው? እስር ቤት እያለሁ በሌሎች የመጎብኘት መብቴን የነፈገው ስርዐት ዛሬ ደግሞ የጠያቂነት መብቴን እየነፈገው ነው፡፡ ሙሉውን ቀን ሊባል በሚችል መልኩ ስለፖለቲካ አሳሪዎቻችን ጉዳይ እያሰብኩ ስብሰለሰል ዋልኩ፡፡ የእኔና የሌሎች በርካቶች መብሰልሰል ምክንያት የሆኑት የኢህአዴግ ባለስልጣናት ደግሞ በአሉን ምክንያት በማድረግ ፍትህ እያዛቡበተ፣ እያሰሩትና እየገደሉት ላሉት ህዝብ የመልካም ምኞት መግለጫቸዉን ሲያዥጎደጉዱለት ዋሉ፡፡ ይህንን የኢህአዴግ ምኞትና ተግባር መራራቅ እያሰብኩ እያለሁ “ኢህአዲግን ለመለወጥ የምንፈልግ ሰዎች ምኞትና ተግባርስ ምን ይመስላል? ” የሚል ጥያቄ ሽው አለብኝ፡፡ ጥያቄው በርካታ መልሶች ቢኖሩትም በዚህ ጽሁፍ ለማቅረብ የመረጥኳቸው ግን ሁለቱን ብቻ ነው፡፡
አጉል ህልመኞች በዚህ ስርዓት ተጠቃሚ በመሆናቸው ብቻ የሌሎችን ወገኖቻቸውንና የሀገርን ጉዳት ማየት ካልቻሉ ወይም ካልፈለጉ ሆዳሞችና በህወሓት የዘረኝነት መርዝ ከተበከሉ ጥቂቶች በቀር የኢህአዴግን መሰንበት የሚፈልግ ዜጋ ስለመኖሩ እጠራጠራለሁ፡፡ በተለያዩ አጋጣሚዎች የማገኛቸዉ ሰዎች ምኞትም የስርዓት ለውጥን ማየት ነው፡፡ ነገር ግን “እነዚህ ሁሉ ሰዎች የሚፈልጉትን ለውጥ ለማየት ምን አይነት አስተዋፅኦ እያደረጉ ነው?” ብለን ብንጠይቅ የምናገኘው ምላሽ አስደሳች አይደለም፡፡
አንዳንድ ለዉጥ ፈላጊዎች ቁጭ ብሎ ከመመኘት በቀር ለለዉጡ መምጣት የሚያደርጉት ምንም ነገር የለም፡፡ ለምን አንዳች ነገር እንደማያደርጉ ስትጠይቋቸው ከምታገኟቸዉ መልሶች መሃከል “እነዚህን መዥገሮች እሱ ይንቀላቸዉ እንጂ በሰው ሃይልማ የሚሆን አይደለም፤ ህዝቡን ከፋፍለውታል እኮ ምን ማድረግ ይቻላል? . . .” የሚሉት ይገኙበታል፡፡ እነዚህ ሰዎች ምንም እንዳይሰሩ ያደረጋቸዉ ትልቁን ምክንያት ጠጋ ብላችሁ ስትመረምሩ ግን ፍርሃት ሆኖ ታገኙታላችሁ፡፡ ፕ/ር መሳይ ከበደ “The Impasse of Fear in Ethiopia and the Necessity of Comprehensive struggle ” በተሰኘ ፅሑፋቸዉ እንዳስቀመጡት ፍርሃት የጨመደደው ህዝብ ሁሌም ምንም ላለማድረጉ የሚያቀርባቸው በርካታ ምክንያቶች ይኖሩታል፡፡
ሌሎቹ ለዉጥ ፈላጊዎች ደግሞ ለዉጥ ሊያመጡ የሚችሉ እንቅስቃሴዎቸን በማድረግ ረገድ ከላይኞቹ የተሻሉ ቢሆኑም የጀመሩትን መጨረስ ግን የማይሆንላቸው ናቸው፡፡ እያደረጉ በነበረዉ እንቅስቃሴ ሳቢያ አንዳች ችግር ሲደርስባቸው ከመንገዳቸው ይወጣሉ፡፡ “በዚህኛው አመተምህረት በተደረገው ምርጫ ሳቢያ ለእስር ተዳርጌ ነበር፤ በዛኛው ወቅት በተደረገው ሰልፍ ላይ ተገኝቼ ተደብድቤያለሁ” ማለት ይቀናቸዋል፡፡ አሁንስ? ስትሏቸው ግን መልሳቸው “ጎመን በጤና” ነው፡፡ እንደነዚህ አይነቶቹ ሰዎች መጀመሪያዉኑ እየታገሉት የነበረውን መንግስት ግፈኝነት በሚገባ ያወቁት አይመስሉም፡፡
የቆረጡ ለዉጥ ፈላጊዎች እነዚህኞቹ አስቀድሞ ከተጠቀሱት ጋር የለዉጥ ፍላጎታቸው ቢያመሳስላቸውም ለውጥን ለማምጣት የሚያደርጉት እንቅስቃሴ መኖሩና ቁርጠኝነታቸው ደግሞ የተለዩ ያደርጋቸዋል፡፡ “እሱ ያመጣዉን እሱ እስኪመልሰው” በማለት እጃቸውን አጣጥፈው አይቀመጡም፡፡ ለለውጡ እዉን መሆን የሚችሉትን ሁሉ ያዋጣሉ፡፡ ከነዚህ ሰዎች መሀከል በግንባር ቀደምትነት ሊጠቀስ የሚገባው ጋዜጠኛ እስክንድር ነጋን መዉሰድ ይቻላል፡፡ እስክንድር ለለዉጡ ያለውን ሁሉ እየከፈለ ያለ ሰው ነው፡፡ ወደስምንት ጊዜ ያህል ሲታሰርና ሲፈታ፣ የመፃፍ መብቱን ሲገፈፍ፣ ሲደበደብ፣ ንብረቱ ሲወረስና ከሚወዳት ባለቤቱና ልጁ ጋር በአካል መለያየት ግድ ሲለዉ ሁሉ በአላማው ከመጽናት ውጭ ለአፍታ እንኳን ሸብረክ ሲል አልታየም፡፡ እስክንድርና መሰሎቹ ዲሞክራሲ እንዲሰፍንና ነፃነት እንዲገኝ ካስፈለገ ከምኞት ባለፈ ስራና መስዕዋትነት እንደሚጠይቅ ገብቷቸዋል፡፡ ለገባቸው እውነት ደግሞ እየኖሩ ነው፡፡ እነ እስክንድር ይሄን ሁሉ መስዕዋትነት ሲከፍሉ ታዲያ ሁኔታው ያማያማቸው ሆኖ አይደለም፡፡ ህመሙን ጥርሳቸውን ነክሰው እየቻሉ እንጂ!
አቶ ኤፍሬም ማዴቦ “ከዊሃ እስከ ኦምሃጀር-አንድ ሰሞን ከአርበኞች ጋር” በሚል ርዕስ በቅርቡ ባስነበቡን ጽሑፋቸዉ የአርበኞች ግንቦት 7 ጦርን ለመቀላቀል ከአሜሪካን ሀገር ከተደላደለ ኑሮዋቸው ተነስተው ሲሄዱ ይሰማቸው የነበረዉን ከሚወዱት ልጃቸው የመለየት ህመም በዉብ አገላላፅ ተርከዉልናል፡፡ አቶ ኤፍሬም አውሮፕላን ማረፊያ ድረስ ሊሸኛቸው የመጣዉን የ17 አመት ልጃቸውን ሲሰናበቱ “ልጄ ይሄን ማድረግ አልፈልግም ነገር ግን ማድረግ አለብኝ” ያሉት ፊታቸው በእንባ እየታጠበ ነበር፡፡ የማይፈልጉትን ነገር ለማድረግ እራሳቸዉን ያስገደዱበትን ምክንያት የገለጹት “የምወደውን አንድ ልጄንና ጥሩ ስራዬን ደህና ሁኑ ብዬ በረሃ የገባሁት ሃገሬ ዉስጥ ፍትህ፣ ነፃነት፣ እኩልነትና ዲሞክራሲ አብቦ ለማየት ነው” በማለት ነው፡፡
ጋዜጠኛ እስክንድርና አቶ ኤፍሬም ምንም እንኳን ለውጥን ለማምጣት የሚሄዱበት መንገድ ለየቅል ቢሆንም ሁለቱም ግን ለለውጡ ያላቸውን ሁሉ ለመስጠት ተዘጋጅተዋል፡፡ አንደኛቸው ለውጡ ግድ ብሎአቸው ቤታቸው እስርቤት ሲሆን ሌላኛቸው ዱርቤቴ ብለዋል፡፡ ሁለቱም ከሚወዷቸው ወንዶች ልጆቻቸው ጋር ተለያይተዋል፡፡ ሁለቱም ለውጥ በምኞት ብቻ እንደማይመጣ ያውቃሉና እራሳቸው ሄደው ይገናኙት ዘንድ በተለያየ መንገድም ቢሆን በጉዞ ላይ ናቸው፡፡
በመጨረሻም
በኢትዮጵያ እኩልነት ዴሞክራሲ ነፃነትና ፍትህ እንዲሰፍን የምንመኝ ሁላችን ከቀን ህልማችን መንቃትና ምኞቶቻችንን ወደ ተግባር ለመለወጥ መንቀሳቀስ ያስፈልገናል፡፡ ከመንቀሳቀስ ያገደን ፍርሃታችን ከሆነ በቀደመው ንዑስርዕስ ስር የጠቀስኩት የፕ/ር መሳይ ጽሑፍ ፍርሃትን ለመዋጋት የሚያስቀምጠው አንድ መፍትሄ አለ፡፡ ድርጊት! ራሳችንን ለፈሪነት የተመደብን አድርገን የምንቆጥርና በሌሎች ደፋርነት መንፈሳዊ ቅናት የሚያድርብን ሰዎች ካለን ፕ/ሩ የጠቀሱት የፈላስፋው አርስቶትል ሃሳብ ሳይጠቅመን አይቀርም፡፡ አርስቶትል “ጀግና ለመሆን ጀግንነትን መለማመድ ያስፈልጋል” ይለናል፡፡ ለአርስቶትል ድፍረት እንደሌሎቹ የሞራል እሴቶች ሁሉ አብሮን የሚወለድ እምቅ ሃይል ሲሆን እውን ለመሆንና ለመዳበር እንዴሎቹ እሴቶች ሁሉ ልምምድ ያስፈልገዋል፡፡ አስፈላጊዉ ጥንቃቄ እንደዳለ ሆኖ እስኪ እስከዛሬ ያላደረግነዉን አንድ ድፍረት የተሞላበት ድርጊት እናድርግ፡፡ ፕ/ሩ እንደሚሉንና እኔም እንደማምነው ድርጊት ስኬትን ያመጣል፡፡ ስኬቱ የቱንም ያህል ትንሽ ቢሆን በራስ መተማመንን ይወልዳል፡፡ በራስ በተማመን ሲኖር ደግሞ ፍርሃት ይጠፋል ወይም ችግር ሊሆን በማይችልበት ደረጃ ዝቅ ይላል፡፡
ከፍርሃታችን ወጥተን እንቅስቃሴ በማድረግ ላይ ሳለን ከኢህአዴግ በሚወረወርብን ዱላ ተሰብረን ከመንገዳችን ላለመውጣት ደግሞ የገዢዉን ፓርቲ ማንነት ጠንቅቆ ማወቅና ቢያንስ የስነልቦና ዝግጅት ማድረግ ያስፈልጋል፡፡ ለማንጠብቀው ነገር አንዘጋጅም፡፡ ያልተዘጋጀንበት ነገር ደግሞ ሁሌም ይጥለናል፡፡ በመሆኑም የምንታገለው ስርዓት ስልጣኑን ላለማጣት የቱንም አይነት ጭካኔ የተሞላው እርምጃ እንደሚወስድ ማወቅና ለዛም እራስን ማዘጋጀት ግድ ይላል፡፡ ደግሞስ ኢህአዴግ ምን ሊያደርገን ይችላል? ሊያደርግብን የሚችለው ሁሉ አስቀድሞም ከአፈር በታች እንዲዉል የተወሰነበት ስጋችን ላይ አይደለምን?
መልካም አዲስ አመት!
መስከረም 3/ 2008

International Press Freedom Awards Zone 9 Bloggers, Ethiopia

$
0
0

In April 2014, Ethiopian authorities arrested six bloggers affiliated with the Zone 9 collective. The bloggers–Abel Wabella, Atnaf Berhane, Mahlet Fantahun, Natnail Feleke, Zelalem Kibret, and Befekadu Hailu–were charged with terrorism.
cp

The Zone 9 blogging collective was formed in May 2012 in response to the evisceration of the independent press and the narrowing of space for free expression. The name, “Zone 9,” is derived from the zones in Kality Prison, the main jail where Ethiopia’s political prisoners, including several journalists, are held. While Kality Prison is organized into eight different zones, the bloggers refer to the entire country as “Zone 9” because of Ethiopia’s lack of democratic freedoms, one of the bloggers told CPJ.

The collective is made up of nine bloggers–the six named above, and Soleyana S Gebremichael, Endalk Chala, and Jomanex Kasaye, all of whom are in exile. Soleyana has been charged in absentia.

In July 2015, weeks before U.S. President Barack Obama visited the country, Ethiopian authorities released Mahlet and Zelalem.

The Zone 9 bloggers were arrested along with three other journalists–editor Asmamaw Hailegeorgis and freelancers Tesfalem Waldyes and Edom Kassaye, who were later released. The initial charges against the group included working with international human rights organizations and taking part in email encryption and digital security training. The group was subsequently charged with terrorism.

Since 2009, when Ethiopia’s anti-terror law was implemented, the government has used the sweeping legislation to imprison more than a dozen critical journalists, according to CPJ research. In 2012, blogger Eskinder Nega was sentenced to 18 years in prison and Woubshet Taye to 14 years, both on terrorism charges. CPJ’s 2014 prison census found that Ethiopia was the fourth worst jailer of journalists in the world, with at least 17 journalists behind bars. Ethiopia also ranked fourth on CPJ’s 2015 list of the 10 Most Censored Countries.

With the motto “We Blog Because We Care,” the Zone 9 collective has voiced concerns over domestic issues, including political repression, corruption, and social injustice. The collective’s posts were frequently blocked inside Ethiopia, but gained a following with Ethiopians in the diaspora, according to local reports. Their posts on Facebook solicited some 12,000 responses a week, reaching 200,000 during a four-part “campaign” they ran on Facebook.

By awarding the Zone 9 bloggers with its International Press Freedom Award, CPJ recognizes the important role that bloggers play in environments where traditional media are weak or have been all but shuttered by financial hardship and direct or indirect state attacks.

Country facts:

Ethiopia released at least six journalists from prison in 2015, but is still holding around a dozen journalists in jail in relation to their work.
In May 2015, the ruling Ethiopian People’s Revolutionary Democratic Front (EPRDF) won 100 percent of the vote.
In 2014, at least eight independent publications were shut down, according to CPJ research.
Between 2013 and 2014, in response to the continued government crackdown on the media, more than 40 journalists fled into exile from Ethiopia.
Significant work:
The Zone 9 Blog
An account from some of the Zone 9 bloggers’ prison experiences

Stevie Wonder does an impromptu freestyle at an Ethiopian Restaurant during an Ethiopian New Year Celebrati

$
0
0

Stevie Wonder does an impromptu freestyle at an Ethiopian Restaurant during an Ethiopian New Year Celebrati…..Stevie Wonder does an impromptu freestyle at an Ethiopian Restaurant during an Ethiopian New Year Celebrati

ላምብ፤ የበግ ለምድ ለብሶ የመጣው ተኩላ ፊልም (ከሕይወት እምሻው)

$
0
0

ዘ ጋርዲያን <<ያሬድ ዘለቀ የሀገሩን ባህልና ወግ በሚያስደንቅ ሁኔታ አይቶ ያሳየበት ድንቅ ፊልም›› ብሎ ያወደሰው ላምብ ወይም ዳንግሌ በካን ፊልም ፌስቲቫል የ 68 አመት ጉዞ ለመጀመሪያ ጊዜ በይፋ ተመርጦ የታየ የኢትዮጵያ ፊልም ነው፡፡ ትላንት ፊልሙ በኤድና ሞል ሲኒማ እየታየ መሆኑን ስሰማ ሄጄ እስካየው ቸኮልኩ፡፡ ማታ ሄጄ ከማየቴ በፊት ስለፊልሙ በተለያዩ ድረ ገፆች ላይ በአመዛኙ በፈረንጆች የተፃፉ እጅግ ብዙ ሙገሳዎችን ሳነብ ቆይቼ ጉጉቴ ከፍ ባለበት ሰአት እዚሁ አዲስ አበባ ከእኔ በፊት ያዩት ጓደኞቼ የተሰማቸውን ያሉባቸውን ፅሁፎች ፌስቡክ ላይ አገኘሁ፡፡ የፊልም ባለሙያ የሆነው ዳዊት የተባለ ወዳጄ ፊልሙን <<….ግራ የሚያጋባ፣ አሰልቺ ….. ገፀባህሪያቱ ከአከባቢያቸው ጋር ክፉኛ የተነጠሉ ከመሆናቸው የተነሳ ‹‹ካንጋሮዎችን ሰሜን ተራራ ላይ እንደማየት›› ሆኖብኛል ….›› ብሎ ባነበብኩት ጊዜ ‹‹ምነው ጨከነበት›› ባሰኙኝ ቃላት የታጨቀ አስተያየቱን ፅፏል፡፡ ሌሎች ጓደኞቼ ያሉትን አየሁ፡፡ ሁሉም ‹‹እኔ አልወደድኩትም፣ አንቺ ግን ሂጂና ለራስሽ እይው›› አሉኝ፡፡ እናም ሄድኩ፡፡ ፊልሙን ላላያችሁትና ለምታዩት ሰዎች ክብር ሲባል የታሪክ ዝርዝር ውስጥ አልገባም ግን የተሰማኝ ይሄ ነው፡፡ [caption id="attachment_3636" align="aligncenter" width="325"]Yared Zeleke Yared Zeleke[/caption]
1. ‹‹በእንግሊዝኛ አምሳል የተፈጠረ አማርኛ››
ከዚህ በፊት እንዳየነው፣ እንደውም ትንሽ ባስ ባለ ሁኔታ- ውጪ ሀገር አድገውና ኖረው በሚመጡ ‹‹ኢትዮጵያውያን›› ፀሃፊዎችና አዘጋጆች እንደተጻፉና እንደተዘጋጁ ፊልሞች ሁሉ ፊልሙ ላይ ያሉ ምልልሶች እጅግ ይቀፋሉ፡፡ አርቴፊሻል ናቸው፡፡ ምክንያቱም ፊልሙ በእንግሊዝኛ ታስቦና ተፅፎ ወደ አማርኛ የተመለሰ ምልልሶችና እና ንግግሮች ድሪቶ ነውና፡፡
በእንግሊዝኛ አምሳል የተፈጠረ አማርኛ የሚያወሩት በገጠር የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ልቋቋመው የማልችለው ህመም ፈጥረውብኛል፡፡ እስቲ በፈጠራችሁ የትኛው የገጠር ልጅ ነው በጉን ‹‹አዝናለሁ እዚህ በማደርሽ …›› ብሎ የሚናገር? ‹‹የነጻነት ትኬታችንን ለማግኘት የሚያስፈልገን 120 ብር ብቻ ነው ›› የሚል? ‹‹የትኛዋ የገጠር ልጃገረድ ናት እናቷን ‹<እንዲህ ልትናገሪኝ መብት የለሽም ›› የምትል? የትኛዋስ ገጠር የምትኖር እናት ናት ልጇን ‹‹‹ደሞ ብለሽ ብለሽ እንደ ሴተኛ አዳሪ በዚህ ሰአት ገባሽ!›› የምትል….? ያማል፡፡ እጅግ ያማል፡፡ — ይሄ ሁሉ ሲሆን ሃይ ባይ ሲጠፋ ደግሞ የበለጠ ያማል! እንዴት በፊልሙ ላይ የተሳተፉ አንጋፋ የሚባሉ እዚሁ ተወልደው፣ እዚሁ አድገው ፣እዚሁ ሲተውኑ የኖሩ ተዋንያን ‹‹የለም የእኛ ሰው እንዲህ አያወራም›› ብለው ለመናገር አይዳዳቸውም! እንዴትስ ፀኃፊ እና አዘጋጁ ከአስር አመት እድሜው ጀምሮ በባእድ ሀገር እንደመኖሩ ‹‹እንዴት ነው…ይሄ ነገር ልክ ነው…?ይሄ አባባል በአማርኛ ስሜት ይሰጣል…?››ብሎ ደህና ሰው ሊያማክር፣ ብሎም ቀጥሮ ሊያሳይ አያስብም? ያሬድ ከካን ፊልም ፌስቲቫል ይልቅ ፊልሙን አዲስ አበባ ማሳየቱ ፍርሃት እንዳሳደረበት ተናግሯል ሲባል አንብቤያለሁ፡፡ ልክ ነው፡፡ እዚህ ያለነው ቋንቋውን እና ባህሉን የምንረዳ ሰዎች ስለሆንን ሊፈራ ይገባ ነበር! ከቋንቋው አኞነት በተጨማሪ ሲያሳቅቀኝ ያመሸው በፊልሙ ላይ የገቡ ፍፁም ስሜት የማይሰጡና እጅግ ግራ የሚያጋቡ አንዳንድ ንግግሮች ናቸው፡፡ ከብዙ ነገር አንድ ምሳሌ ብቻ ላምጣ፡፤ የፊልሙ ዋና ገፀ ባህሪ የሆነው ትንሹ ልጅ ኤፍሬም ከዘመዶቹ ጋር ለመኖር አዲስ ቤት ሲመጣ ያገኛትን የስጋ ዘመዱን ሴት ልጅ ‹‹መቀነትሽ ያምራል›› ሲላት መስማት እጅግ ይረብሻል፡፡ ከዚያ በላይ የሚረብሸው ግን ኤፍሬምና ይህች ዘመዱ ሲለያዩ በመኪና መስኮት መቀነቷን ፈትታ መስጠቷ ነው፡፡ በሀገራችን ‹‹መቀነት መፍታት›› ምን ማለት እንደሆን ያሬድ ያውቅ ይሆን! 2. ህዘቡ ተኩላ ሆኖ ተስሏል በትንሹ ኤፍሬምና በሚወዳት በጉ ጩኒ ዙሪያ በሚያጠነጥነው ፊልም ላይ ከ ጅማሬ እስከ ፍፃሜ ኤፍሬም በጉ እንዳትታረድበት መላ ሲቀይስና ‹‹መከራውን ሲያይ›› የፊልሙ ፀሃፊና አዘጋጅ በኤፍሬም ዙሪያ ያለውን ማህበረሰብ፣ በተለይም ቤተሰቡን የኤፍሬምን በግ ለመብላት ያሰፈሰፈ ተኩላ ብቻ አድርጎ ስሎታል፡፡ ቤተሰቡ ፍቅር የሌለው፣ ለሆዱ ብቻ የሚያስብ፣ እንግዳን የሚንቅና ለጥቅም ብቻ የቆመ አድርጎ ያሳየናል፡፡ በተለይም በረሃብ የሞተች እናቱን ትዝታ ተሸክሞ ለመጣ ምስኪን የአደራ ዘመድ ልጅ አንድ የገጠር ቤተሰብ ሊሰጥ የሚችለው ነገር ይሄ ብቻ ነው ተብሎ መሳሉ የደራሲና አዘጋጁን ጠባብ እይታ የሚሳይ እና የሚያሸማቅቅ ነው፡፡ በድህነት ውስጥ ፍቅር የሚመግበውን፣ በረሃብ ውስጥ ፍቅርና ለልጅ መሳሳትን የሚያሳየንን፣ በከፋ ረሃብ ጊዜ እንኳን ‹‹ከብቶቼን አላርድም›› ብሎ ከእንሳሶቹ በፊት የሚረግፈውን ማህበረሰብ በእንዲህ ያለው ‹‹ለፊልሙ ሲባል በግድ በተፈጠረ›› ቤተሰብ መወከል ወንጀል ሆኖ ታይቶኛል፡፡ 3. በመጨረሻም….ፊልሙ በፈረንጆች የተወደደበት ምክንያት ገብቶኛል! ሆሊውድ ኬንያዊቷ ሉፒታ ኒዮንጎን ኦስካር የሸለማት የሚፈልጋት ቦታ ስላገኛት ነው፡፡ ባሪያ ሆና ስለሰራች፡፡ ሆሊውድ ዴንዘል ዋሽንትተንን በሙስና የተዘፈቀ ጥቁር ፖሊስ ሆኖ ሲሰራ ኦስካር የሸለመው የሚፈልገው ቦታ ስላገኘው ነው፡፡ ሆሊውድ ሆቴል ርዋንዳን መታየት ያለባቸው የምንጊዜም 250 ምርጥ ፊልሞች መካከል ያስቀመጠው የሚፈልገው ቦታ ስላገኘው ነው፡፡ የአፍሪካን ሰቆቃ የሚተርክ ስለሆነ፡፡ ቋንቋውን እና ባህሉን ለማያውቅ ሰው ላምብ ግሩም ፊልም ሆኖ ሊታይ ይችላል፡፡ በተለይም አፍሪካን እና ኢትዮጵያን አንድ ሳጥን ውስጥ አስቀምጦ ከዚያ የወጣ ነገር ለማየት ፈቃደኛ ባልሆነ ምእራባዊ አይን ላምብ ግሩም ፊልም ነው፡፡ የሚፈለገውን ሁሉ ያሟላል፡፡ ከምእራቡ አለም በዘመናት ወደ ኋላ ቀርተው ሳሎናቸው ውስጥ በእንጨት ማገዶ የሚያበስሉ ሰዎችን ያሳያል፡፡ የአፈር ወለል ያለው ደሳሳ ጎጆ ውስጥ የሚኖሩ ችጋራም ኢትዮጵያውያንን ያሳያል፡፡ በረሃብ የሞተች እናትን ታሪክ ይናገራል፡፡ በግ አርደው ለመብላት ያሰፈሰፉ ረሃብተኛ ኢትዮጵያውያንን አጉልቶ እንካችሁ ይላል፡፡ ይሄ ለእነሱ አውነት ነው፡፡ ይህ ለእነሱ ልክ ነው፡፡ ስለዚህም ወደውታል፡፡ ምእራባውያን ስለ እኛ የሚሰሩትን ፊልም መቆጣጠር አንችል ይሆናል፡፡ ‹‹የእናንተ ነኝ›› የሚል ሰው ግን እነሱን ሆኖ ፣በእነሱ አይን አይቶን፣ እንደነሱ ሲፅፈን እና ሲያበጀን ማየት ያሸማቅቃል፡፡ ያሳቅቃል፡፡ እናውቃለን- ደሃ ነን፡፡ እናውቃለን – ረሃብተኞች ነን፡፡ ኢትዮጵያውያን ግን ደሃ እና ረሃብተኞች ብቻ አይደለንም፡፡ በድህነታችን እና ረሃባችን ውስጥ እሴት ያለን ሰዎች ነን፡፡ ራበን ብለን አደራ የምንሰለቅጥ ህዝቦች አይደለንም፡፡ ስለ ረሃብና ድህነት በሚተርክ ፊልም ውሰጥ ስብእናችን፣መተሳሰብና እንደ ህዝብ ያለንን ማንንት ለማሳየት የሚያስፈልገው ችሎታ ብቻ ነው፡፡ ያሬድ እና አጃቢዎች ያንን ለማድረግ የሚያስችል የፊልም ጥበብን እንደ ተካኑ ማየት አይከብድም፡፡ ግን አያውቁትም ወይም የሚያውቁን አልጠየቁም፡፡ እናም፤ ዘ ጋርዲያን <<ያሬድ ዘለቀ የሀገሩን ባህልና ወግ በሚያስደንቅ ሁኔታ አይቶ ያሳየበት ድንቅ ፊልም›› ብሎ ያወደሰው ላምብ ወይም ዳንግሌ ፊልም በካን ፊልም ፌስቲቫል ታይቶ የተወደደው ለእነሱ የሚፈልጉትን ኢትዮጵያ ስላቀረበ ይሆናል፡፡ እኔ እና መሰሎቼ ግን ታመንበታል፡፡ ያሬድ ዘለቀ ተወድሶበታል፡፡ እኛ ግን አፍረንበታል፡፡


የዴምሕት መሪ ሞላ አስገዶምና ኢትዮጵያ መግባት_VOA Amharic

$
0
0

Molla Asgedom, leader of TPDM defects and returned to …..Molla Asgedom, leader of TPDM defects and returned to Ethiopia….Molla Asgedom, leader of TPDM defects and returned to Ethiopia
Ethiopia

Facebook users will soon be able to ‘DISLIKE’ friends’ posts, says Mark Zuckerberg

$
0
0

The creator of the social networking site said people wanted to express empathy with their friends
Facebook users will soon be able to ‘dislike’ posts and pictures on their feeds, it was announced today.

dislike-main
The social networking site’s founder Mark Zuckerberg revealed Facebook is working on the feature following years of requests for the function.

He said users of the site wanted to express feelings other than ‘liking’.

Zuckerberg gave examples of times when users might like to ‘dislike’ posts, such as when people post about family members who have died.

As reported by business insider.com, Zuckerberg told a question and answer session at Facebook’s headquarters: “I think people have asked about the dislike button for many years.
“Today is a special day because today is the day I can say we’re working on it and shipping it.”

Zuckerberg said he believes users of the site don’t want to use ‘dislike’ to be negative towards other people.

He said: “What they really want is the ability to express empathy.”

He said Facebook had been working on the feature for some time and was hoping to launch it in the near future.

No date was given for when it would be available.

Source mirror.co.uk

Ziggy Zaga – Jilo – (Official Music Video) – New Ethiopian Music 2015

$
0
0

Ziggy Zaga – Jilo – (Official Music Video) – New Ethiopian Music 2015…..Ziggy Zaga – Jilo – (Official Music Video) – New Ethiopian Music 2015…Ziggy Zaga – Jilo – (Official Music Video) – New Ethiopian Music 2015

Comedian Kibebew Geda and Other Artists Comment on Seifu and Veronica Wedding

$
0
0

Comedian Kibebew Geda and Other Artists Comment on Seifu and Veronica Wedding,,,,,,,በሰሜን አሜሪካ ያሉ ኢትዮጵያውያን አርቲስቶች ስለ ሰይፉ ፋንታሁን እና ባለቤቱ ቬሮኒካ ኑረዲን ጋብቻን በተመለከተ ያዘጋጁት ልዩ ዝግጅት። የክበበውን አስቂኝ አስተያየትና ምክር ብርሃኑ ተዘራ፣መሰፍን በቀለ ፣ይሁኔ በላይ ፣ፋሲል ደሞዝ፣ተቦርነ በየነ፣ሄኖክ ነጋሽ እና ሌሎች አርቲስቶችን መልዕክት ይመልከቱት።

South Sudan peace accord workshop continued in Addis Ababa-VOA Amharic

$
0
0

South Sudan peace accord workshop continued in Addis Ababa-VOA Amharic…….የደቡብ ሱዳናዊያን የሚስማሙባቸውም የማይስማሙባቸውም ነጥቦች አሉ,,,,,South Sudan peace accord workshop continued in Addis Ababa-VOA Amharic

ሰኞ ምሽት ወጣቷን በጥይት የገደለው የፌዴራል ፖሊስ አባል በራሱ ላይ የግድያ ሙከራ አደረገ

$
0
0

አንድ የፌዴራል ፖሊስ አባል ለቡ አካባቢ በሚገኝ መዝናኛ ቤት ውስጥ ሰኞ ምሽት አንዲት ወጣት መግደሉ ተሰማ፡፡ ግለሰቡ ራሱን ለማጥፋት ቢሞክርም ተርፎ በሕክምና ላይ ይገኛል፡፡

ሰሎሜ ጉልላት የተባለችው የ20 ዓመት ወጣት ከጓደኛዋ ጋር በመሆን በለቡ ኮንዶሚኒየም ቤቶች አካባቢ በሚገኝ የጓደኛቸው መዝናኛ ውስጥ በመዝናናት ላይ እያሉ ነው ከተጠርጣሪው ገዳይ ጋር የተገናኙት፡፡

87a16f70d957081bb7afbd21ff2124bc_L

ለጊዜው ስሟን መናገር ካልፈለገችው ጓደኛዋ መረዳት እንደተቻለው፣ የፖሊስ የደንብ ልብስ የለበሰው ግለሰብ ከዚህ ቀደም ሰሎሜን አስቸግሮ ከሚያውቅ ግለሰብ ጋር በሚዝናኑበት ባር ውስጥ እንደነበር ትናገራለች፡፡ ሁለቱ ሴት ጓደኛሞች መዝናኛ ባሩ ውስጥ የነበራቸውን ቆይታ አጠናቀው ከመውጣታቸው በፊት፣ ወደ መፀዳጃ ቤት ለመግባት ተስማምተው መሄዳቸውን ታስታውሳለች፡፡ ክፍሉ ራሱን የቻለ መዝጊያ ኖሮት መፀዳጃ ክፍሎቹም ራሳቸውን የቻሉ መሆናቸውን የገለጸችው የዓይን እማኟ፣ አንዱን ክፍል በሚከፍቱበት ወቅት ዩኒፎርም የለበሰው ፖሊስ ውስጥ ሆኖ ስላዩት ይቅርታ መጠየቃቸውን ትገልጻለች፡፡

ይቅርታቸውን ተቀብሎ እንደወጣ እነሱ ወደ መፀዳጃ ክፍሎቹ ገብተው ከደቂቃ በኋላ ሲወጡ የዋና ክፍሉን በር ቆልፎ ፖሊሱ መፀዳጃ ክፍል ውስጥ እንደጠበቃቸው አስረድታለች፡፡ ወደ ሰሎሜ ተጠግቶ ‹‹አንቺ ሰው የማታናግሪው ለምንድነው?›› ብሎ በጥፊ እንደመታትና እንደወደቀች የገለጸችው የሟች ጓደኛ፣ እሷ በሁኔታው ተደናግጣ ወደ መፀዳጃ ክፍሉ ገብታ መቆለፏን ትናገራለች፡፡ በክፍሉ ውስጥ እንዳለች የተኩስ ድምፅ መሰማቱን፣ የማቃሰት ድምፅ ስትሰማ መውጣቷን ገልጻለች፡፡

ጓደኛዋ ሰሎሜም ሆነች ፖሊሱ ወድቀው እንዳየቻቸው ሰው እንዲደርስላት ብትጮህም፣ ለደቂቃዎች ያህል ማንም እንዳልደረሰ ትናገራለች፡፡

በኋላ ከደረሰችላት አንዲት እንስት ጋር በመሆን እስትንፋሷ የነበረውን ጓደኛዋን ለመርዳት እየሞከረች ሳለ፣ ፖሊሶች እንደደረሱና በሥፍራው ወደሚገኝ ጤና ጣቢያ በፒክ አፕ መኪና ይዘዋት መሄዳቸውን፣ ነገር ግን የጓደኛዋ ሕይወት ማለፉን ገልጻለች፡፡

ተጠርጣሪው የፖሊስ ባልደረባ ጭንቅላቱን በጥይት መትቶ ራሱን ለማጥፋት ቢሞክርም ሕይወቱ ባለማለፉ የሕክምና ዕርዳታ እየተደረገለት ነው፡፡

ጉዳዩን በተመለከተ ከፖሊስ መረጃ ለማግኘት የተደረገው ጥረት አልተሳካም፡፡ ይሁን እንጂ ተጠርጣሪው ገና በሕክምና ላይ በመሆኑ ፖሊስ ቃሉን እንዳልተቀበለ ምንጮች ገልጸዋል፡፡

የወጣት ሰሎሜ የቀብር ሥነ ሥርዓት ማክሰኞ መስከረም 4 ቀን 2008 ዓ.ም. በለቡ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ተፈጽሟል፡፡
ምንጭ ሪፖርተር ጋዜጣ

CPJ award bestowed to Zone9 of Ethiopia_VOA Amharic

$
0
0

CPJ award bestowed to Zone9 of Ethiopia_VOA Amharic….ዞን ዘጠኝ ተሸለሙ
የዞን ዘጠኝ ፀሐፊዎች የዓለም አቀፍ የፕሬስ ነፃነት ተሸላሚ ሆኑ፡፡,,CPJ award bestowed to Zone9 of Ethiopia_VOA Amharic


UEFA Champions League Highlights & Review – Match Day 1 – 15.09.2015 HD

$
0
0

UEFA Champions League Highlights & Review – Match Day 1 – 15.09.2015 HD……UEFA Champions League Highlights & Review – Match Day 1 – 15.09.2015 HD

Ethiopia: Tilahun Gugssa’s Emotional Speech at Seble Tefera Memorial Service in VA – September 2015

$
0
0

Ethiopia: Tilahun Gugssa’s Emotional Speech at Seble Tefera Memorial Service in VA – September 2015…አርቲስት ሰብለ ተፈራን ለማሰብ በArlington Virginia በተዘጋጀው የሻማ ማብራትና የጸሎት ዝግጅት ላይ አንጋፋው አርቲስት ጥላሁን ጉግሳ ያደረገው ልብ የሚነካ ንግግር

Obama, Zuckerberg and NASA back Muslim teen, 14, arrested in school after his homemade alarm clock was mistaken for a bomb – as police confirm they won’t press charges

$
0
0

DALLAS (AP) — A 14-year-old Muslim boy became a sensation on social media Wednesday after word spread that he had been placed in handcuffs and suspended for coming to school with a homemade clock that teachers thought resembled a bomb.
11999964_1499714197009321_518029962_n

Police declined to seek any charges against Ahmed Mohamed, but that did little to tamp down criticism of police and school officials or suspicions that they had overreacted because of the boy’s religion.

Mohamed was pulled from class Monday and taken to a detention center after showing the digital clock to teachers at his suburban Dallas high school.

Irving Police Chief Larry Boyd said the clock looked “suspicious in nature,” but there was no evidence the boy meant to cause alarm at MacArthur High School. Boyd considers the case closed.

In a matter of hours, the clock made Mohamed a star on social media, with the hashtag #IStandWithAhmed tweeted nearly 750,000 times by Wednesday afternoon.

Groups including the American Civil Liberties Union condemned what they called the school’s heavy-handed tactics.
“Instead of encouraging his curiosity, intellect and ability, the Irving (school district) saw fit to throw handcuffs on a frightened 14-year-old Muslim boy wearing a NASA T-shirt and then remove him from school,” Terri Burke, executive director of the ACLU in Texas, said in a statement.

The White House also weighed in.

In a tweet, President Barack Obama called Mohamed’s clock “cool” and said more kids should be inspired like him to enjoy science, because “it’s what makes America great.”

Asked if bias was involved, White House press secretary Josh Earnest said it was too early “to draw that direct assessment from here.” But, he added, Mohamed’s teachers had “failed him.”

“This is an instance where you have people who have otherwise dedicated their lives to teach our children who failed in that effort, potentially because of some things in their conscience and the power of stereotypes,” he said.

The boy was invited to participate in an astronomy night the White House is organizing sometime next month with premier scientists.

In a post to his site, Facebook founder Mark Zuckerberg said, “Having the skill and ambition to build something cool should lead to applause.”

“Ahmed, if you ever want to come by Facebook, I’d love to meet you,” Zuckerberg posted. “Keep building.”

The teen explained to The Dallas Morning News that he makes his own radios, repairs his own go-kart and on Sunday spent about 20 minutes before bedtime assembling the clock using a circuit board, a power supply wired to a digital display and other items.

Mohamed’s father, Mohamed Elhassan Mohamed, told the Morning News that his son “just wants to invent good things for mankind. But because his name is Mohamed and because of Sept. 11, I think my son got mistreated.”

The boy’s family said Mohamed was suspended for three days. It was not clear if he will be allowed to return to school now that police have declined to pursue the matter.

School district spokeswoman Lesley Weaver declined to confirm the suspension, citing privacy laws. Weaver insisted school officials were concerned with student safety and not the boy’s faith.

The police chief said the reaction to the clock “would have been the same regardless” of his religion.

“We live in an age where you can’t take things like that to school,” Boyd said.

Boyd said police have an “outstanding relationship” with the Muslim community in Irving and that he would meet the boy’s father Wednesday to address any concerns.

This spring, the city council endorsed one of several bills under discussion in the Texas Legislature that would forbid judges from rulings based on “foreign laws” — legislation opponents view as unnecessary and driven by anti-Muslim sentiment.

The Council on American-Islamic Relations is reviewing the action against Mohamed.

“This all raises a red flag for us: how Irving’s government entities are operating in the current climate,” Alia Salem, executive director of the council’s North Texas chapter, told the Morning News.

4th Power raise the roof with Jessie J hit | Auditions Week 1 | The X Factor UK 2015

$
0
0

4th Power raise the roof with Jessie J hit | Auditions Week 1 | The X Factor UK 2015……4th Power raise the roof with Jessie J hit | Auditions Week 1 | The X Factor UK 2015

Mogachoch EBS Latest Series Drama – S02E43- Part 43

$
0
0

Mogachoch EBS Latest Series Drama – S02E43- Part 43…EBS Latest Series Drama Mogachoch – Part 43- የሞጋቾች መሳጭ ተከታታይ የEBS ድራማ ክፍል 43 ተመልከቱት

Viewing all 3774 articles
Browse latest View live