Quantcast
Channel: Kalkidantube
Viewing all articles
Browse latest Browse all 3774

አትሌቶች ተቃውሞ ያነሳሉ በሚል ፍርሃት የኦሮሚያ ክለቦች ውድድር ተሰረዘ።

$
0
0

wer
በመላው ኦሮሚያ በተነሳው ተቃውሞ ምክንያት 3ሺህ አትሌቶች ከተለያዩ ኦሮሚያ ክለቦች የሚካፈሉበት ውድድር በአሰላ ሊካሄድ አትሌቶች አሰላ ከገቡ በኃላ ተሰረዘ።
ዛሬ ይጀመር የነበረው ውድድር ላይ አትሌቶቹ በመላው ኦሮሚያ መንግስት ልዩ ጦር አዝምቶ ወገኖቻችንን እየገደለና እያሰረ መሆኑን በመቃወም በመክፈቻ ሰነስርዓት ላይ ጥቁር ለብሰው ሊገቡ እንደሆነ ስለተደረሰበት ውድድሩ ሊሰረዝ ችሏል።የቃልኪዳን ቲዩብ ምንጮች እንደገለጹት የአሰላ ህዝብ በዚህ አጋጣሚ ተጠቅሞ ተቃውሞውን ይገልጻል በሚል ፍርሃት እና ተቃውሞው በአትሌቶቹ መደገፉ ለህዝብ ተጨማሪ መነሳሳት ይሆናል በሚል ከፌደራል በቀጥታ በመጣ ትእዛዝ ሊሰረዝ መቻሉን ገልጸውልናል።
አትሌቶቹ ሰሞኑን በልምምድ ሜዳዎች ላይ”መግደል ይቁም፣ገበሬው አባታችንን የሚያፈናቅል ማስተር ፕላን እናወግዛለን፣የ6ብር ግምት ለገበሬው ሰጥቶ በሚሊዮን የሚሸጥበት የመሬት ዝርፍያ ይቁም”የሚሉ ተቃውሞ ሲያሰሙ ቆይተዋል።

በሰላማዊ መንገድ ተቃውሞውን የሚያሰማው የኦሮሞ ሕዝብን ለመግደል ዛሬ የተንቀሳቀሰው የገዢው መንግስት ወታደሮች።

በሰላማዊ መንገድ ተቃውሞውን የሚያሰማው የኦሮሞ ሕዝብን ለመግደል ዛሬ የተንቀሳቀሰው የገዢው መንግስት ወታደሮች።


አንድ ወር ሊሞላው ሁለት ቀን የቀራው በመላው ኦሮሚያ በተነሳው ተቃውሞ መንግስት የኅይል እርምጃ መውሰድና መግደል የቀጠለ ሲሆን በትላንትናው ቀን ብቻ 25ሰዎች ተገድለዋል።እስካሁን ከ50በላይ ሰዎች የተገደሉ ሲሆን የኦሮሚያ ፖሊሶች ወገኔን አልገልም በማለታቸው ልዩ ኮማንድ ፖስት በፌድራል መንግስት ተዋቅሮ ድምጹን እያሰማ ያለውን ህዝብ ከመግደል የሚጀምር እርምጃ ሊወስዱ ከተለያዩ የጦር ካንፖች ወደህዝቡ ተልኳል።
ኢሰብዓዊ ጭፍጨፋ እየተደረገበት ያለው ህዝብ መሳርያ ከታጠቁ ኃይሎች ጋር ተናንቆ በ152ቦታዎች ድምጹን እያሰማ ነው።

Viewing all articles
Browse latest Browse all 3774

Trending Articles