* “እናቴ ወደ ሀገር ስትገባ አብሬ እገባለሁ ! ” ብላ እንደ ወጣች ቀረች …
የታዋቂዋ አርቲስት የማሪቱ ለገሰ ልጅ ወ/ት ወደሬ ከበደ በጅዳ ተቀበረች ! ሳውዲ ጅዳ የዛሬ ሁለት ሳምንት በአደረባት ህመም ከዚህ አለም በሞት የተለየችው ወ/ት ወደሬ ከበደ ከአሰሪዎቿ ቤት ሁና ህክምናዋን ስትከታተል ቆይታለች ። ደካክማ ከስራ ቦታ አበራ ትኖርባቸው ወደ ነበረበት ቤተሰቦችዋ መጣች ። ” ለምን እስክትደካክሚ ጠበቅሽ ?” ብለው የተደናገጡ ቤተሰቦች ሲያነጋግሯት ወደ ሀገር መግባት እንደምትፈልግ አሳውቃቸው በዚያው ቀን ወደ ሀገር የመግቢያ ሰነድ ለመጠየቅ ወደ ጅዳ ቆንስል አመሩ ። ቤተሰቦችዋ በህመም የተጎሳቆለችውን ወ/ት ወደሬ ከበደን ይዘው ወደ ጅዳ ቆንስል ያመሩት ቤተሰቦች መንገድ ላይ አስደጋጭ ሁኔታ ተፈጠረ ፣ እህት ወደሬ ትንፋሿ አቆመ ፣ ሰውነቷ ቀዘቀዘ … ህዳር የአርቲስት ማሪቱ ለገሠ ልጅ ወ/ት ወደሬ እስከ መጨረሻው አንቀላፋች frown emoticon ህዳር 20 ቀን 2008 ዓም …
ይህን የተረዱ የተጨነቁ ቤተሰቦች በዚያው ቅጽበት በተፈጠረው አስደንጋጭ ሀዘን ግራ ተጋብተው መንገዳቸውን ወደ ጀመሩት የጅዳ ቆንስል አደረጉ … ሬሳውን በመኪና ላይ አስቀምጠው ሬሳ ማስቀመጫ ፈቃድ ለማውጣት የወጡት የወረዱበት ድካም ሀዘንተኞቹን ጎዳቸው … ከሰዓታት እንግልት በኋላ የወደሬ አሰሪዎች ባደረጉላቸው ትብብር ሬሳውን በክብር ማሳረፍ መቻላቸው ተገልጾልኛል። ከዚያም በቀጣይ ቀናት አስፈላጊ የመቅበሪያ ውክል ከቤተሰብ በኩል ከውጭ ጉዳይ አስልከው በሁለት ሳምንት ጊዜ ለቀብር አስፈላጊውን ሁሉ አሟልተው መጨረሳቸውን መረጃውን ያቀበሉኝ የቤተሰቡ አባላት አሳውቀውኛል …
ከወ/ት ወደሬ ከበደ ጋር 11 ልጆቿን ያጣችው ታዋቂዋ የባህል ድምጻዊ ማሪቱ ለገሰ አሁን የቀራት አብዱ የሚባል ልጇ ሲሆን ዛሬ የቀብር ሥነ ሥርዓቷ የተከዎነው ወ/ት ወደሬ የአብዱ ታላቅ እህቱ እንደ ነበረች ተጠቁሟል ። እህት ወደሬ ከአርቲስት እናቷ ከማሪቱ ለገሠ ጋር ትኖር የነበረ ሲሆን የዛሬ 20 ገደማ ድምጸ አርቲስት ማሪቱ ለገሠ ወደ አሜሪካ ስትሔድ እሷም ወደ ሳውዲ አረቢያ ጅዳ መምጣቷን በቅርብ የሚያውቋት አጫውተውኛል ። እኒሁ የቤተሰብ አባላትና የቅርብ ወዳጆች በማከልም ” ወደሬ ለኑሮዋ የሚጎላት ነገር ባይኖርም እናቴ ወደ ሀገር ስትገባ አብሬ እገባለሁ ! ” ብላ ስትጠባበቅ ባደረባት የስኳር ህመም እንደወጣች በሞት ከዚህ አለም መለየቷን በሀዘን በተጎዳ ስሜት በዝርዝር አስተድተውኛል !
የተወዳጇ ድምጸ መረዋ አቀንቃኝ የማሪቱ ለገሠ ልጅ ወ/ት ወደሬ ከበደ የቀብር ሥነ ሥርዓት ታህሣሥ 3 ቀን 2008 ዓም ከምሽቱ የኢሻ ጸሎት በኋላ ልዩ ስሙ ባብ ሸሪፍ በሚገኝ ቢን ማዕሩፍ በተባለ መስጊድ የቅርብ ወዳጅ ዘመዶችና አብሮ አደጎቿ በተገኙበት ተፈጽሟል !
የተወዳጇ ድምጸ መረዋ አቀንቃኝ ለማሪቱ ለገሠ ፣ ለቤተሰብና ለዘመድ አዝማድና ለወዳጆቻቸው መጽናናትን እመኛለሁ ! የሟችንም ነፍስ ይማር !
ታህሣሥ 4 ቀን 2008 ዓም
( ፎቶው የተወዳጇ ድምጸ መረዋ አቀንቃኝ የማሪቱ ለገሠ ነው)