ከትላንት በስቲያ በሲልቨር እስፕሪንግ እመቤት የተባለች ኢትዮጵያዊት በደረሰባት የመኪና አደጋ ህይወቷ አልፏል። የሁለት ልጆች እናት የሆነችው እመቤት የነርስ ባለሙያ ነበረች። አደጋውን ያደረሰው አሽከርካሪ ቢሰወረም ነገር ግን በስፍራው የነበሩ ሃበሾች ተከታትለው ፎቶ በማንሳትና የመኪናውን ታርጋ በመፃፍ ለፖሊስ ሪፖርት ባደረጉት መሰረት በዛሬ እለት በቁጥጥር ስር ውሏል።….
ዛሬ ከቀትር በኋላ በዲሲ የሃበሻ ሰፈር መንገድ ዳር አንድ ወጣት እንቅልፉን ይለጥጣል። በዚህ ሃይለኛ የፀሐይ ንዳድ እንዲህ አቅሉን ስቶ የተኛበት ምስጢሩ አደንዛዥ እፅ በመውሰዱ እንደሆነ የሚያውቁት ነገሩኝ። «ፒዛሮ» የተባለ ከቻይና የሚገባ አደንዛዥ እፅ አለ። የዲሲ መንግስት በቅርቡ አዲስ ህግ አውጥቷል። ይህ እፅ ሲሸጥ የተገኘ 10ሺህ ብርና 5 አመት እስር ይከናነባል። ምክንያቱም አደንዛዥ እፁ በሰውነት ውስጥ ያለውን ኦክሲጅን በማውረድ ለህልፈት ስለሚዳርግ ነው። ሶስት ሃበሾች ሞተዋል። 15 ጥቁር አሜሪካውያን በአንድ ስፍራ አስክሬናቸው ተነስቶዋል። በገዛ ነፍስ ላይ መፍረድ!?…