በተለያዩ የኦሮሚያ ክልሎች በህዳር ወር ህዝባዊ ተቃውሞ ቀጥሏል።በምዕራብና በምስራቅ የኦሮሚያ ክልሎች በሚገኙ ከተሞች የመንግስት ወታደሮች ክልላችንን ለቀው ይውጡ፣ግድያ ፣እስራትና ድብደባ ይቁም የሚሉ ጥያቄዎች በማሰማት ላይ ናቸው። በመኢሶ ሲካሄድ የሰነበተው ተቃውሞ ሰባተኛ ቀኑን መያዙን የዘገበው ቪኦኤ ተመሳሳይ ተቃውሞዎችም
ትላንት በጉደር ከተማ ተቀስቅሶ ወታደሮች ጥቃት መፈጸማቸውን ገልጿል።በምስራቅ ወለጋ በወለጋ ዩኒቨርሲቲ እንዲሁም በሆሮ ጉድሩ በተካሄደ ህዝባዊ ተቃውሞ ወታደሮች ተኩሰው የአንድ ወጣት ህይወት ማለፉን የ12 አመት ልጅ ጭንቅላቱን እንደተመታ እማኞችን ጠቅሶ ቪኦኤ ዘግቧል።
በተለያዩ የኦሮሚያ ክልሎች ኢህአዴግ ገዳይ ነው።ከስልጣን ይውረድ ጥያቄዎች ለጥምቀት ክብረ በአል የወጣው ህዝብ መጠየቁን ወታደሮችም ህዝቡ ላይ መተኮሳቸውን በዘገባው ውስጥ ገልጿል።ሙሉ ዘገባውን ያዳምጡ።
↧
በኦሮሚያ ክልል ተቃውሞ ቀጥሏል-VOA Amharic
↧