በስልጣን ላይ ያለው መንግስት ጠቅላይ ሚንስትር አቶ ኃይለማሪያም ደሳለኝ በትጥቅ ትግል መንግስት ለመቀየር የሚንቀሳቀሱ ተቃዋሚ ኃይሎች ወደ ሰላማዊ መንገድ ቢመጡ ይሻላቸዋል ሲሉ ያቀረቡትን ጥሪ ተቃዋሚዎች አጣጣሉት።
የኦሮሞ ነፃነት ግንባር ቃል አቀባይ አቶ ዳውድ ኢብሳ ለቪኦኤ በሰጡት ምላሽ “የትጥቅ ትግል ውስጥ የገባነው ፈልገን ሳይሆን መብታችንን ለማስከበር ነው አቶ ኃይለማርያም እኛን የማስተማር አቅም የላቸውም” ብለዋል ። በቅርብ አዲስ አበባ ለድርድር ሄደው ተባረው የተመለሱት አቶ ሌንጮ ባቲ ጥሪውን ደግፈዋል።ዝርዝር ቃለምልልስ ያድምጡ።
↧
የኃይለማሪያም ደሳለኝ የትጥቅ ትግል አቁሙ ጥሪና የቡድኖቹ ምላሽ-VOA Amharic
↧