Quantcast
Channel: Kalkidantube
Viewing all articles
Browse latest Browse all 3774

አፍሪካ ፊልም አካዳሚ አዋርድ ላይ”ሦስት ማዕዘን”ፊልም በሽልማት ተንበሸበሸ (ቴዎድሮስ ጌታሁን)

$
0
0

ትላንት ማምሻውን በውቢቷ ፖርት ኤልዛቤት ከተማ በተካሄደው አስራ አንደኛው የ አፍሪካ ፊልም አካዳሚ አዋርድ ላይ፣ በ
ስምንት ዘርፎች እጩ ሆኖ የቀረበው የ ቴዎድሮስ ተሾመ “ሦስት ማዕዘን” ፊልም በ ሦስት ዘርፎች አሸናፊ በመሆን ታሪክ ሰራ።
Triangle going to America ወይም ሦስት ማዕዘን የመጀመሪያ ሽልማቱን ያገኘው ምርጥ የማጀቢያ ሙዚቃ
በሚለው ዘርፍ ሲሆን በዚህም ድምፃዊ ጌትሽ ማሞ ወደ መድረክ በመውጣት የተዘጋጀለትን ሽልማት ተቀብሏል
11209425_10153604035928468_4045435456848260961_n
በዚህ ዘርፍ የናይጄሪያዎቹ ታዋቂ ፊልሞች A place in the star, Iyore እንዲሁም የ አንጎላው Queen of angole እና
የሞሪታኒያው Timbectu እጩ ሆነው ቢቀርቡም ሦስት ማዕዘን ፊልምን ያጀበው ጌትሽ ማሞን ሚቆመው አልተገኘም ቀጥሎ በምርጥ ተዋናይ ዘርፍ በተካሄደ ውድድር አሁንም ሦስት ማዕዘን ፊልም አሸናፊ መሆን ችሏል
በዚህ ዘርፍ የደቡብ አፍሪካው I number number, የናይጄሪያው October, የ ካሜሮኑ Leperdes እና የ ኮትዲቫሩ Run ፊልሞች ላይ በመሪ ተዋናይነት የተወኑ አርቲስቶች ቀርበው በመጨረሻም ኢትዮጵያዊው አክተር ሳምሶን ታደሠ ቤቢ አሸናፊ መሆን ችሏል
ሽልማቱን ለመቀበል ወደ መድረክ የወጣው ሳምሶን ንግግሩን በአማርኛ ያደረገ ሲሆን በዚህም “…ስለሁሉም የረዳኝን
እግዚአብሔር አመሰግናለሁ እዚህ ደረጃ ደርሳለሁ ብዬ በህይወቴ አስቤ አላውቅም ነበር አሁን ደስታዬ ወደር የለውም
በመጨረሻ ዓለም ወደደም ጠላም አፍሪካ አንድ ትሆናለች” ብሏል
12019983_10153604125178468_8386492795609769509_n

የ አማርኛውን ንግግር ወደ መድረክ በመውጣት ወደ እንግሊዝኛ የተረጎመለት የፊልሙ ደራሲ’ና ፕሮዲውሰር ቴዎድሮስ ተሾመ
ነበር ቀጥሎ በ ሽማግሌዎች ወይም በ እንግዶች ምርጮ የ አፍሪካ ምርጥ ፊልም በሚል ዘርፍ Le president ካሜሩን Timbectu ሞሪታኒያ October ናይጄሪያ Run ኮትዲቮር እና I number number ደቡብ አፍሪካ በ እጩ ዘርፍ ቀርበው አሁንምኢትዮጵያዊው ሦስት ማዕዘን ፊልም አሸናፊ መሆን ችሏል ይህን ሽልማት ለመቀበል ደራሲ እና ፕሮዲውሰር ቴዎድሮስ ተሸሞ መሪ ተዋንያኖቹ ሳምሶን ታደሠ ቤቢ እና ሰለሞን ቦጋለ እንዲሁም የ ማጀቢያ ሙዚቃውን የሠራው ድምፃዊ ጌትሽ ማሞ ወደ መድረክ በመውጣት ሽልማቱን ከተቀበሉ በኋላ የ ዶክተር አርቲስት ጥላሁን ገሠሠን ኢትዮጵያ ሀገሬ የሚለውን ዜማ በጋራ ከተመልካቹ ጋር በማቅረብ ታዳሚውን ማዝናናት ችለዋል።


Viewing all articles
Browse latest Browse all 3774

Trending Articles