በእናቷ ኢትዮጵያዊ በአባቷ ኤርትራዊ የሆነችው ድምጻዊት ዘውዲ ሓብቲ አወሎም ለመጀመርያ ግዜ ወደኢትዮጵያ ልትሄድ ነው።
ከልጅነቷ የጀመረው ሙዚቀኛ የመሆን ፍላጎቷ ድምጻዊ በሆነው አባቷ እገዛ ዛሬ የደረሰችበት ደረጃ የደረሰችው ዘውዲ የተወለደችው ኒውዮርክ ሲሆን ያደገችው ኒውጀርሲ ነው።
በዩቲዮብ ሙዚቃዋ ከ16ሚሊዮን በላይ በሚሆኑ ተመልካቾች የታየላት ሲሆን የራሷን ሙዚቃዎች በተለያዩ ቦታዎች ከማቅረቧም ሌላ ከታዋቂ ድምጻዊያን ጀርባ ተቀባይ ድምጻዊ ሆና ሰርታለች ።የ23 ዓመቷ ዘውዲ የእናት አገሯ ኢትዮጵያን ለመጀመሪያ ግዜ ለማየት ጉዞ መጀመሯ ልዩ ስሜት እንደተሰማት ገልጻለች ።ከሙዚቃዎቿ አንዱ የሆነውን በአማርኛና በእንግሊዝኛ የተጫወተችውን “into the night “እንጋብዛችሁ።
↧
ድምጻዊት ዘውዲ ለመጀመርያ ግዜ ወደኢትዮጵያ ልትሄድ ነው
↧